ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, March 4, 2019

ከእዚህ በፊት ያልሰሙት የኢትዮጵያ ተፅኖ ፈጣሪነት በአፍሪካም ሆነ በዓለም የነበረበትን ከፍተኛ ደረጃ የሚያሳይ ድንቅ ቃለ መጠይቅ (ቪድዮ)

ጉዳያችን / Gudayachn
መጋቢት 5/2011 ዓም (ማርች 5/2019 ዓም)

ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ኒውዮርክ ላይ እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር 1956 ዓም ( እ ኤ አ 1963 ዓም) የሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ 
- ስለ ቻይና  ተንብየዋል፣
- አፍሪካን ከቅኝ ግዛት ለማውጣት ጦር ሊጠቀሙ እንደሚችሉ አውሮፓን አስጠንቅቀዋል፣
- ነጮች አፍሪቃውያን ከቅኝ ግዛት ከወጡ በኃላ በአፍሪካ እንዴት መኖር እንዳለባቸው ጠቁመዋል፣
- ከመከላከያ ሚኒስትርነት እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይልቅ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ቻንስለርነት ለምን እንደመረጡ ገልጠዋል።
- ጥቁርነት በአሜሪካ ስቃይ በሆነበት ዘመን በአሜሪካ የውስጥ ጉዳይ ገብተው በአደባባይ አሜሪካንን ወቅሰዋል። 

ባጭሩ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ምን ያህል ተፈሪ እና ተፅኖ ፈጣሪ እንደነበር በእዚህ ቃለ መጠይቅ መረዳት ይቻላል።አውሮፓውያን በአፍሪካ የነበራቸውን የቅኝ መግዛት ሕልም ትንሽ ለማራዘም ቢፈልጉም የንጉሡ ፈጣን አካሄድ በተለይ ብዙዎች የአፍሪካ ሀገሮች በቅኝ ግዛት በነበሩበት ዘመን እ ኤ አ  በ1963 ዓም የአፍሪካ አንድነትን መስረተው አፍሪቃውያንን ከቅኝ ግዛት ቀንበር ማስጣላቸው ቅኝ ገዢዎች እስከመጨረሻው ጥርስ አልነከሱም ማለት አይቻልም።ዛሬም በንጉሡ ላይ አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ስም ለማጥፋት የሚሞክሩ የቅኝ ገዢዎች ቂም አስፈፃሚ አይደሉም ማለት እንዴት ይቻላል?



ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...