Monday, March 4, 2019

ከእዚህ በፊት ያልሰሙት የኢትዮጵያ ተፅኖ ፈጣሪነት በአፍሪካም ሆነ በዓለም የነበረበትን ከፍተኛ ደረጃ የሚያሳይ ድንቅ ቃለ መጠይቅ (ቪድዮ)

ጉዳያችን / Gudayachn
መጋቢት 5/2011 ዓም (ማርች 5/2019 ዓም)

ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ኒውዮርክ ላይ እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር 1956 ዓም ( እ ኤ አ 1963 ዓም) የሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ 
- ስለ ቻይና  ተንብየዋል፣
- አፍሪካን ከቅኝ ግዛት ለማውጣት ጦር ሊጠቀሙ እንደሚችሉ አውሮፓን አስጠንቅቀዋል፣
- ነጮች አፍሪቃውያን ከቅኝ ግዛት ከወጡ በኃላ በአፍሪካ እንዴት መኖር እንዳለባቸው ጠቁመዋል፣
- ከመከላከያ ሚኒስትርነት እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይልቅ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ቻንስለርነት ለምን እንደመረጡ ገልጠዋል።
- ጥቁርነት በአሜሪካ ስቃይ በሆነበት ዘመን በአሜሪካ የውስጥ ጉዳይ ገብተው በአደባባይ አሜሪካንን ወቅሰዋል። 

ባጭሩ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ምን ያህል ተፈሪ እና ተፅኖ ፈጣሪ እንደነበር በእዚህ ቃለ መጠይቅ መረዳት ይቻላል።አውሮፓውያን በአፍሪካ የነበራቸውን የቅኝ መግዛት ሕልም ትንሽ ለማራዘም ቢፈልጉም የንጉሡ ፈጣን አካሄድ በተለይ ብዙዎች የአፍሪካ ሀገሮች በቅኝ ግዛት በነበሩበት ዘመን እ ኤ አ  በ1963 ዓም የአፍሪካ አንድነትን መስረተው አፍሪቃውያንን ከቅኝ ግዛት ቀንበር ማስጣላቸው ቅኝ ገዢዎች እስከመጨረሻው ጥርስ አልነከሱም ማለት አይቻልም።ዛሬም በንጉሡ ላይ አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ስም ለማጥፋት የሚሞክሩ የቅኝ ገዢዎች ቂም አስፈፃሚ አይደሉም ማለት እንዴት ይቻላል?



ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

No comments:

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...