Monday, August 25, 2014

''የአፄ ኃይለ ስላሴ ውርስ ጠንካራ እና ሕጋዊ እንደሆነ ቀጥሏል'' የቻይናው ሲሲቲቪ በቅርቡ ከለቀቀው ፊልም ግርጌ ከተፃፈው ማስታወሻ። የቻይናው ሲሲቲቪ ''የአፍሪካ ገፅታ'' በተሰኘው ፕሮግራሙ ''ኃይለ ስላሴ የዘመናዊት ኢትዮጵያ መስራች አባት'' (Haile Selassie: The pillar of Ethiopia) በሚል ርዕስ ስር የሰራው አስደናቂ ጥናታዊ ፊልም ለዘመናችን ባለስልጣናትም ሆነ ትውልድ አስተማሪ ነው።Faces Of Africa - Haile Selassie: The pillar of Ethiopia, part 1 & 2 CCTV (ቪድዮውን ይመልከቱ)

ማንኛውም መሪ መቶ በመቶ ትክክል ሊሰራ አይችልም ግን ከ 80 በመቶ በላይ መልካም ሥራ ቢሰራ የቀረው ''ስህተት'' የተባለውም ለሀገሩ ካለው ፍቅር የሰራው ከሆነ ይህ መሪ ታላቅ ነው።
አፄ ኃይለ ስላሴ ከስልጣን ከወረዱ በመጪው መስከረም 2/2007 ዓም ሙሉ አርባ ዓመት ይሞላቸዋል።ዛሬም ግን ታሪክ እየጎለጎለ የሚነግረን ለኢትዮጵያ ታላቅ ሥራ የሰሩ መሪ መሆናቸውን ነው።
የምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሃን ብዙ ብለዋል።እንደ ''ታይም'' አይነት መፅሄቶች''የመቶ ዓመቱ ታላቅ ተፅኖ ፈጣሪ'' ብለው አወድሰዋቸዋል።ለነገሩ የታሪካችን አካል የሆኑ መሪን ማንነት የባዕዳን መገናኛ ብዙሃን እና ፀሐፍያን ሲመሰክሩልን ብቻ የምናምን ሲያብጠለጥሉ ደግሞ ዝቅ የማድረግ አባዜ ሊጠናወተን አይገባም።አፄ ኃይለሰላሴን በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ዘመናዊ ታሪክ ላይ ያላቸውን አሻራ የዘገቡልን በሁሉም ርዕዮተ ዓለም ውስጥ ያሉ ሃገራት መሆናቸው ጉዳዩ ምን ያህል ተአማኒ መሆኑን አመላካች ነው።ለምሳሌ የዛሬውን የታሪክ ዘገባ የቀረበው  የቻይናው ታዋቂው  ቴሌቭዥን ''ሲሲ ቲቪ'' ነው።ቪድዮውን ይመልከቱት።

Haile Selassie I (1892 -1975)
ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...