ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, June 30, 2014

የኢትዮጵያ የቀድሞ ዘመናዊ የጦር ሰራዊትን ታሪክ ሳንዘክር ስለ ኢትዮጵያ ማውራት አንችልም

የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጦር ሰራዊት መሰረቱ በዳግማዊ ምንሊክ ዘመን ይጣል እንጂ በተደራጀ መልክ የተመሰረተው ከፋሽሽት ኢጣልያ መባረር በኃላ መሆኑን በርካታ ድርሳናት ያስረዱናል።ዛሬ ቀና ብለን ስለ ኢትዮጵያ መናገር የቻልነው በጥንት አባቶቻችን ተጋድሎ ብቻ አይደለም።የቀድሞ ዘመናዊ የጦር ሰራዊት ገድልም ትልቅ አስተዋፆ አለበት።ሱማልያ ''ቁርስ ድሬዳዋ ምሳ አዲስ አበባ'' በሚል መፈክር በ1969 ዓም በከፈተችብን ጦርነት ከሞቃዲሾ በምታስተላልፈው የአማርኛ ራድዮ ፕሮግራም ፎክራብን ነበር።ምስራቃዊውን የሀገራችንን ክፍል ይዛ ነበር።
በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሚሊሻ ከመደበኛ ሰራዊት ጋር እልህ አስጨራሽ ውግያ አድርጎ ነፃነታችንን እና የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ያስከበረው የቀድሞ ዘመናዊ የጦር ሰራዊት ነው።ኢትዮጵያውያን ብዙ ያልገቡን፣ክብር መስጠት ሲገባን ክብር ያልሰጠናቸው ክቡራን አሉን።
ክብር ለቀድሞ ዘመናዊ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት! የኢትዮጵያ የቀድሞ ዘመናዊ የ ጦር ሰራዊትን ታሪክ ሳንዘክር ስለ ኢትዮጵያ ማውራት አንችልም።



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።

የሰው ደም እየፈሰሰ መከላከያና የአማራ ክልል ታጣቂ ኃይል አይነጋገር የሚሉት በውጪ ሀገር ሶፋ ላይ የተቀመጡት መሆናቸውን ልብ ይሏል። የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ...