ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, August 19, 2012

¨ጉዳያችን¨ በ አንድ አመቷ

ጉዳያችን ጡመራ መጫጫር ከጀመረች እነሆ አንድ አመቷን ደፈነች። እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ :-
  • ሰላሳ ሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ተነስተዋል፤
  • ከ አስር ሺ ጊዜ በላይ (ከ ሰላሳ አምስት ሃገሮች በላይ ውስጥ ነዋሪ በሆኑ) አንባብያን  መከፈቱን ለማወቅ ችያለሁ፤
  • የ ጡመራው ከፋቾች ብዛት በደረጃ ኖርዌይ፣ኢትዮዽያ፣ሰሜን አሜሪካ በቀን ውስጥ ብዙ ጊዜ በመክፈት ሲጠቀሱ፤ ከ መካከለኛው ምስራቅ የ አረብ ኢምሬትስ እና እስራኤል ከ እስያ ሩስያ፤ ከ አውሮፓ ጀርመን እና እንግሊዝ፤ ከ አፍሪካ ኢትዮዽያን አስከትለው ደቡብ አፍሪካ እና ኡጋንዳ ይጠቀሳሉ።
  • አስተያየትን በተመለከተ የ ጡመራው  ከፋቾች በጣም ቁጥብ ናቸው።እስካሁን ከ ሰላሳ ሁለቱ ርዕስ ጉዳዮች አስተያየት የተሰጠው ብዛት ሰባ አራት ብቻ ነው። በእርግጥ በ ኢሜይል የሚላኩት በጣም አስፈላጊ ሃሳቦች ሆነው አግኝቻቸዋለሁ። ለምሳሌ ፎቶዪን ¨ከበድ¨ አለ የሚል ሃሳብ ከሰነዘሩልኝ ጀምሮ በቅርብ የተያያዙትን የ ¨የ ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካን ሊንክ¨ እና የ እንግሊዝኛው  ¨ኖርዌይ ፖስት¨ ጋዜጣ ሊንክ መለጠፉን እስካሞገሱልኝ ድረስ አስተያየት ለሰጣችሁኝ እግዚአብሔር መካሪ አያሳጣብኝ እያልኩ አመሰግናለሁ። ፎቶዬን በተመለከተ በትክክልም አምኘበታለሁ እናም ቀይሬዋለሁ።በ መጪው 2005 ዓም እናንተ በ ኢ-ሜልም ጭምር በመምከር እኔ በመሞነጫጨር እንድበረታ በጸሎታችሁ አስቡኝ።
ጌታቸው በቀለ
ኦስሎ

2 comments:

dembelash said...

hi gechow ye bounaw koers ansowel be DEBRETABOWER KEN menaw kolow

Anonymous said...

Berta!!