ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, August 19, 2012

¨ጉዳያችን¨ በ አንድ አመቷ

ጉዳያችን ጡመራ መጫጫር ከጀመረች እነሆ አንድ አመቷን ደፈነች። እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ :-
  • ሰላሳ ሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ተነስተዋል፤
  • ከ አስር ሺ ጊዜ በላይ (ከ ሰላሳ አምስት ሃገሮች በላይ ውስጥ ነዋሪ በሆኑ) አንባብያን  መከፈቱን ለማወቅ ችያለሁ፤
  • የ ጡመራው ከፋቾች ብዛት በደረጃ ኖርዌይ፣ኢትዮዽያ፣ሰሜን አሜሪካ በቀን ውስጥ ብዙ ጊዜ በመክፈት ሲጠቀሱ፤ ከ መካከለኛው ምስራቅ የ አረብ ኢምሬትስ እና እስራኤል ከ እስያ ሩስያ፤ ከ አውሮፓ ጀርመን እና እንግሊዝ፤ ከ አፍሪካ ኢትዮዽያን አስከትለው ደቡብ አፍሪካ እና ኡጋንዳ ይጠቀሳሉ።
  • አስተያየትን በተመለከተ የ ጡመራው  ከፋቾች በጣም ቁጥብ ናቸው።እስካሁን ከ ሰላሳ ሁለቱ ርዕስ ጉዳዮች አስተያየት የተሰጠው ብዛት ሰባ አራት ብቻ ነው። በእርግጥ በ ኢሜይል የሚላኩት በጣም አስፈላጊ ሃሳቦች ሆነው አግኝቻቸዋለሁ። ለምሳሌ ፎቶዪን ¨ከበድ¨ አለ የሚል ሃሳብ ከሰነዘሩልኝ ጀምሮ በቅርብ የተያያዙትን የ ¨የ ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካን ሊንክ¨ እና የ እንግሊዝኛው  ¨ኖርዌይ ፖስት¨ ጋዜጣ ሊንክ መለጠፉን እስካሞገሱልኝ ድረስ አስተያየት ለሰጣችሁኝ እግዚአብሔር መካሪ አያሳጣብኝ እያልኩ አመሰግናለሁ። ፎቶዬን በተመለከተ በትክክልም አምኘበታለሁ እናም ቀይሬዋለሁ።በ መጪው 2005 ዓም እናንተ በ ኢ-ሜልም ጭምር በመምከር እኔ በመሞነጫጨር እንድበረታ በጸሎታችሁ አስቡኝ።
ጌታቸው በቀለ
ኦስሎ

2 comments:

dembelash said...

hi gechow ye bounaw koers ansowel be DEBRETABOWER KEN menaw kolow

Anonymous said...

Berta!!

በውግዘት ውስጥ ላሉት፣አሁንም በድፍረት ለሚሄዱት ለትግራይ የቀድሞ ጳጳሳት አልቅሱላቸው።

 አክሱም ጽዮን በክርስትና ታሪክ ለሁለት ሺህ ዓመታት ያህል ያላየችውን የድፍረት ስራ በቅዱስ ሲኖዶስ በተወገዙት የትግራይ አባቶች እያየች ነው። የእነርሱን አካሄድ እየተመለከተ ዝም ብሎ የሚገለገለው የትግራይ ምዕመን፣ የእዚ...