ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, August 15, 2023

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት እንደሆነ የታመነው የመንግስት ጥቃት በጦር ወንጀለኝነት የሚያስጠይቅ ነው።በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አጣሪ ኮሚቴም ካስፈለገ መቋቋም ያለበትና በድርጊቱ የሚጠየቁትን በትክክል ለፍርድ ማቅረብ ይገባል።


የቪኦኤ አማርኛ አገልግሎት ሙሉ ዘገባ ከስር ተያይዞ ያገኛሉ።

=======
ጉዳያችን
=======


በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት እንደሆነ የታመነው የመንግስት ጥቃት እንደ የፍኖተሰላም ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ለቪኦኤ አማርኛ እንደገለጹት በጥቃቱ እስካሁን 26 መሞታቸው የተረጋገጠና 50 በላይ መቁሰላቸው ተረጋግጧል። ድርጊቱን አስመልክቶ የአሜሪካ ድምጽ ራድዮ የአማርኛው አገልግሎት የዐይን እማኞችን አነጋግሮ ያቀረበው ሪፖርት ደረጃውን የጠበቀ እና በስፍራው የነበረውን ሁኔታ ገለልተኛ በሆነ መልክ የተጠናቀረ ሪፖርት መልክ ያለው ነው።

ይህ ጥቃት እንደየዐይን እማኞች ገልጻ ቀደም ብሎ ድሮን በሰማይ ላይ ከመታየቱና ቃኚ አይሮፕላን ከማለፉ ጋር ተያይዞ እና በአካባቢው ሌላ ምንም ዓይነት የከባድ መሳርያ መጠመድ ባለመኖሩ የዐይን እማኞች የድሮን ጥቃት እንደሆነ እና በፒካፕ መኪናው ዙርያ ያልታጠቁ በርካታ ሰዎች መኖራቸው በግልጽ እየታየ የተፈጸመ ጥቃት መሆኑን በእዚሁ ዘገባ ላይ ነዋሪዎች ለቪኦኤ የአሜሪካ ራድዮ የአማርኛ አገልግሎት ተናግረዋል።

ይህ ማለት ድርጊቱ በጦር ወንጀል የሚያስጠይቅና ይህ እንዲፈጸም ትዕዛዝ ያስተላለፈው ማን እንደሆነ መንግስት መርምሮ ጉዳዩን ለህዝብ መግለጽ ያለበት ጉዳይ ነው። በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አጣሪ ኮሚቴም ካስፈለገ መቋቋም ያለበትና በድርጊቱ የሚጠየቁትን በትክክል ለፍርድ ማቅረብ ይገባል።

የቪኦኤ አማርኛው አገልግሎት ሙሉ ዘገባ ሰኞ ነሐሴ 8፣2015 ዓም (ኦገስት 14፣2023 ዓም)



No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...