ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, August 17, 2023

''አንዱ ሲናገር ሌላው አያቋርጥ!'' የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎች ክፍል ውስጥ የሚነገራቸው እና የሚያከብሩትን መመርያ ፓርላማው ገና አልተለማመደውም።

የተከበሩ አቶ ባያብል ሙላቴ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል።

======
ጉዳያችን
======

በእዚህ ሳምንት የተሰበሰበው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ብዙ ኢትዮጵያውያንን የስብሰባ አካሄዱ ደረጃውን የጠበቀ ሆኖ አላገኘውም።የተጀመረ ሃሳብ አዳምጦ ሃሳቡ ላይ ሌላ ሃሳብ ከመስጠት ይልቅ በማኅበራዊ ሚድያ አሉባልታ በሰሙት ወሬ እራሳቸውን እና የወከሉትን ህዝብ ክብር በማይመጥን ደረጃ ንግግሮችን ሲያቋርጡ እና ሃሳቦችም እንዳይሰጡ ሲሞክሩ ትዝብት ላይ ወድቀዋል።

የተወካዮች ምክርቤት አባላት የተሰበሰቡት ኢትዮጵያውያንን ወክለው ነው። ኢትዮጵያውያንን መወከል ማለት ደግሞ የተከበረ ባሕል፣መከባበርና አስተዋይነት አብሮ ሊታይበት ይገባ ነበር። አንድ የምክር ቤት አባል ወደ ምክርቤቱ ሲገባ የፓርቲዬን ሃሳብ በእጅም በእግርም ብዬ ማሳለፍ ብቻ በሚል ከሃሳብ ሙግት ውስጥ የሚገኝ አዲስ ለሃገር የሚበጅ በጎ ሃሳብ ፈልቅቆ ለማግኘት የሚይስችል ስብዕና ይዞ ካልገባ ከሚቀመጥበት ወንበር ብዙ አይለይም። የሚባለውን ሁሉ እየተቀበለ ለማሳለፍ እንጂ በሃሳብ ለመሞገት ያልተዘጋጀ የፓርላማ አባል እቤቱ ቢቀመጥ እና በሌላ መገናኛ መንገድ ድምጹን መላክም ይችላል።

ህዝብ የፓርላማ አባል የመረጠው እንደራሴ ሆነህ በአፍህ ተናገርልኝ፣ሞግትልኝ በአዕምሮህ እኔን ሆነህ አስበህ ሃሳብ አፍልቅልኝ በማለት እንጂ ሌላው የሚናገረውን አዳምጦ በሚገባ እና አሳማኝ በሆነ ምክንያት ከማቅረብ ይልቅ ህጻናት የማያደርጉትን እየተንጫጫ የሚናገር ሰው እንዲያቋርጥ አይደለም።''አንዱ ሲናገር ሌላው አያቋርጥ!'' የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎች ክፍል ውስጥ የሚነገራቸው እና የሚያከብሩትን መመርያ ፓርላማው ገና ያልለመደው ትንሽ ቆይቶ በሱማሌ የምናየው ዓይነት የፓርላማ መንጫጫት እንዳናይ እየፈራን ነው። ትልቅ ሰው ባትፈሩ፣ልጆች እየተመለከቷችሁ ነው። እነርሱ በትምህርት ቤታቸው አስተማሪ አንዱ ተናግሮ ሳይጨርስ ሌላው አይናገርም! የሚለውን መመርያ ክፍላቸው ውስጥ አይጥሱትም።ከሰሞኑ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የቀድሞው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የጸጥታ ጉዳይ አማካሪ ሲናገሩ የነበረው የፓርላማ አባላት የተባለው ትክክልም ይሁን አይሁን በአጽንዖት የማዳመጥ ትዕግስት የማጣት ሁኔታ በእርግጥም ከተራ ስነምግባርም ባለፈ የተባለውን ሰምቶ በምክንያት የመሞገት የአቅም ውሱንነት የታየበት ነው።

አሁን ያለው ፓርላማ ከኢህአዴግ/ህወሃት ዘመን ፓርላማ ጋር ሲነጻጸር በሰው ኃይሉ የትምህርት ዝግጅትም ሆነ በልምድ የተሻለ እና አንጻራዊ መሻል አለበት ብለው የሚያስቡ ነበሩ።በክርክር ሃሳብ ሰልቶ እንዲወጣ በማድረግ ለሃገር የተሻለውን መንገድ እንድትጠቁሙ የተቀመጣችሁ የፓርላማ አባላት ህዝቡ ውስጥ የሚሰማውን የተለያዩ ሃሳቦች፣ሙግቶች፣ድጋፎችም ጭምር ሲንጸባረቁ ማየት የምንፈልግበት ቦታ ፓርላማ ነው። ፓርላማው የአንድ የፓርላማ አባሉን ሃሳብ ወደደውም ጠላውም ለማዳመጥ እና ተናጋሪው ሲጨርስ ሃሳብ የመስጠት ትዕግስት ካጣ ህዝቡማ ከመነጋገር ይልቅ ዱላ ልምዘዝ ቢል ምን ሊፈረድበት ነው?

አሁንም አልረፈደም። ፓርላማው እንዴት መነጋገር፣መሞገት እና በነጻነት ሃሳቡን የማንሸራሸር መብቱን ቁጭ ብሎ መክሮ ያስተካክል። በ21ኛው ክ/ዘመን ተቀምጠን እንድ የህዝብ ተወካይ ሲናገር ለመስማት የሚያስችል ትዕግስት እንዴት እንደሚገኝ መማሩ እጅግ አስፈላጊ ነው።

በእዚህ ሳምንት የአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማጽደቅ በተተራው ስብሰባ ላይ አቶ ገንዱ አንዳርጋቸው ሲናገሩ የፓርላማ አባላት ላሳዩት ትዕግስት ያጣ የማቋረጥ ሙከራ የምክር ቤቱ አባል የተከበሩ አቶ ባያብል ሙላቴ እንዲህ በማለት አምርረው ገልጸውታል።



No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...