Sunday, January 13, 2019

የጥምቀት በዓል በእዚህ ሳምንት መጨረሻ በመላዋ ኢትዮጵያ እና በባሕር ማዶ ይከበራል።በዓሉ የብሔራዊ አንድነታችን እና መተሳሰባችን አንዱ መገለጫ ነው።

  • ኦስሎ፣ኖርዌይም የበዓሉ ታዳሚ ነች። 
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን  በአደባባይ ከሚከበሩት በዓላት ውስጥ ጥምቀት አንዱ እና ዋናው ነው። ዘንድሮ የሚከበረው የጥምቀት በዓል በያዝነው ሳምንት ከዓርብ ጥር 10/2011 ዓም (ጃንዋሪ 18/2019 ዓም) ከቀትር በኃላ ጀምሮ ታቦታት ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ወጥተው  በመላዋ ኢትዮጵያ እና በባሕር ማዶ በሚገኙ ኢትዮጵያን ዘንድ ይከበራል።በዓሉ የብሔራዊ አንድነታችን እና መተሳሰባችን አንዱ መገለጫ ነው።

በዓሉ በኦስሎ፣ኖርዌይ የኢትዮጵያ ኦ/ተ/መካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያንም በድምቀት ይከበራል።በበዓሉ ላይም የደቡብ አውሮፓ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሚገኙ ሲሆን መምህር ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ከኢትዮጵያ  በስብከተ ወንጌል ያገለግላሉ።

ጥምቀት አዲስ አበባ ቪድዮ (ከዩቱብ ፋይል)

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ፖለቲካ፣ የአፈጀው የአዛውንቶች ክበብ፣ ''ፅንዶ'' እና ቅምጥሎቹ ''ባንዳ'' ዩቱበሮች በአውሮፓና አሜሪካ።

+++++++++++++ ጉዳያችን ወቅታዊ ምጥን +++++++++++++ መንደርደርያ ኢትዮጵያ በዘመን አቆጣጠሯ ስንሔድ የሐያ አንደኛውን ክ/ዘመን የመዠመርያ ሩብ ክፍለዘመን ለማጠናቀቅ ሰባት ዓመታት ብቻ ቀርተዋታል። ያለፈው ሐ...