ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, January 29, 2019

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋዜጣው መግለጫ ሰጡ።

ጉዳያችን / Gudayachn
ጥር 22/2011 ዓም (ጃንዋሪ 29/2019 ዓም)

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን  በአሜሪካና  አውሮፓ ካሉት ሶስት ስቱድዮዎች በተጨማሪ ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ ስቱድዮ እንደሚያስመርቅ አክቲቪስት ታማኝ በየነ፣ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና  አበበ ገላው ዛሬ ጥር 21/2011 ዓም ዋሽንግተን ላይ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

በእዚሁ መግለጫ ላይም ጥር 22/2011 ዓም የጎፈንድ በቀጥታ ስርጭት በዋሽንግተን ሰዓት አቆጣጠር ከቀትር በኃላ ከ2 pm ጀምሮ እንደሚኖር እና የካቲት 9/2011 ዓም በአዲስ አበባ በሚገኘው የሚሊንየም አዳራሽ  የኢሳት 8ኛ ዓመት ልዩ መርሐግብር እንደሚኖር ተገልጧል።

በየካቲት 9/2011 ዓም ከሚደረገው የአዲስ አበባ  መርሃግብር ለመገኘት ወደ ሀገር ቤት ከሚያቀኑት ጋዜጠኞች ውስጥ ከዋሽንግተን አበበ ገላው ፣መሳይ መኮንን፣ ሲሳይ አጌና እና እንግዱ ወልዴ ሲሆኑ ወንድማገኝ ጋሹ ከለንደን  እና ዘላለም ኃይሉ  የሚገኙበት እንደሆነ በመግለጫው ላይ ተገልጧል።በሌላ በኩል ጋዜጠኛ ገሊላ እና መታሰቢያ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ እንደሚገኙም  በመግለጫው  ላይ ተብራርቷል።
ሙሉ መግለጫውን ከስር ይመልከቱ።

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...