ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, May 20, 2018

'' ንቃት፣ትጋት እና ቅንነት ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ወሳኝ ናቸው'' አቡነ ሕርያቆስ በኖርዌይ የመካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሐይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እና የአቡነ ኤልያስ ረዳት አገልጋዮችን ሲሸልሙ የተናገሩት (ቪድዮ)

ጉዳያችን/Gudayachn
ግንቦት 12/2010 ዓም (ሜይ 20/2018 ዓም)

  • የኖርዌይ መካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሐይማኖት ቤተ ክርስቲያን የህንፃ አሰሪ ኮሚቴ አሰራር ናሙና ለሌሎች አጥብያ አብያተ ክርስቲያናት መልካም ናሙና (model) አሰራሮች ስላሉት ከመዋቅር እስከ ስብሰባ አመራር እና ስራዎች ሂደት አንድ ወጥ የሆነ ባለ ጥቂት ገፆች ዝርዝር ማስታወሻ በአነስተኛ መፅሐፍ መልክ ለየትኛውም አጥብያ እንዲረዳ በታሰበ መልክ እንዲያዘጋጁ በእዚህ አጋጣሚ አደራ ማለት እንፈልጋለን።

በኖርዌይ የመካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሐይማኖት ቤተ ክርስቲያን አዲስ የገዛችውን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን አድሳ እና አስባርካ ግንቦት 11/2010 ዓም ታቦታቱን አስገብታለች።በኖርዌይ የኢትዮያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  አገልግሎት ስትሰጥ ከ15 ዓመታት  በላይ ብታስቆጥርም የራሷ ህንፃ ቤተ ክርስቲያን አልነበራትም።ሆኖም ላለፉት ሶስት ዓመታት በተለየ መልክ  የምእመናንን ተሳትፎ ባጎለበተ መልኩ በተደረገው እንቅስቃሴ እና የአቡነ ሕርያቆስ ለአገልግሎት ወደ ኖርዌይ መምጣት፣የእርሳቸው መልካም አስተዳደር፣አመራር እና ጸሎት፣ከሁሉም ቀደም ብሎ ደግሞ የአቡነ ኤልያስ የረጅም ዓመታት ክትትል፣አባታዊ ምክር እና ጸሎት ሁሉ ታግዞ  መንፈሳዊ አገልግሎቱን የበለጠ የሰመረ ከማድረጉም በላይ ቤተ ክርስቲያኒቱ የራሷ ህንፃ እስከመግዛት እና ውስጡን በአዲስ መልካ አድሳ በሊቃነ ጳጳሳት አስባርካ ለመግባት ችላለች።


ይህ በእንዲህ እያለ ግንቦት 12/2010 ዓም ለቤተ ክርስቲያን ህንፃ ግዢ የበኩላቸውን ያገለገሉ ወንድሞች እና እህቶችንን እና ታዳጊ ወጣት ዲያቆናትን አቡነ ኤልያስ እና አቡነ ሚካኤል በተገኙበት በአቡነ ሕርያቆስ አቅራቢነት ከሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ጋር መክረው እንዲሸለሙ አድርገዋል። የሽልማቱን ቪድዮዎች ከእዚህ በታች በክፍል አንድ እና ሁለት ይመልከቱ።የእዚህ አይነቱ አገልግሎት ለሌሎች አጥብያዎች ትምህርት እንደሚሆን አያጠራጥርም።የኖርዌይ መካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሐይማኖት ቤተ ክርስቲያን የህንፃ አሰሪ ኮሚቴ አሰራር ናሙና ለሌሎች አጥብያ አብያተ ክርስቲያናት መልካም ናሙና (model) አሰራሮች ስላሉት ከመዋቅር እስከ ስብሰባ አመራር እና ስራዎች ሂደት አንድ ወጥ የሆነ ባለ ጥቂት ገፆች ዝርዝር ማስታወሻ በአነስተኛ መፅሐፍ መልክ ለየትኛውም አጥብያ እንዲረዳ በታሰበ መልክ እንዲያዘጋጁ በእዚህ አጋጣሚ አደራ ማለት እንፈልጋለን።የእዚህ አይነቱ በፅሁፍ የሚቀመጡ አሰራሮች ወደፊት እየዳበሩ ሄደው ለቤተ ክርስቲያናችን አሰራር ማንዋል ደረጃ ሊጠቅሙ ይችላሉ።ምክንያቱም የችግሮች መፍትሄዎች የሚገኙት ከተጨባጭ የአሰራር ሂደት ውስጥ ከሚያጋጥሙ መሰናክሎች እና እነኛን መሰናክሎች እንዴት እንደተፈቱ ለሌሎች በጽሁፍ በማስቀመጥ ነው።  

ክፍል አንድ  
ቪድዮ በጉዳያችን
ቪድዮ በጉዳያችን

 ክፍል ሁለት  



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments: