በኢትዮጵያ የሚሰሩ የቴሌቭዥን ድራማዎች፣ፊልሞች እና የኤፍ ኤም ራድዮኖች የሚነግሩን ስለ ጥቂቶች ሕይወት ነው።የራድዮ እና ቴሌቭዥን ማስታወቂያዎች ስለ ቅንጡ መኪናዎች እና የቢራ ማስታወቂያዎች ያሳዩናል። እነኝህ ሁሉ ግን የጥቂቶችን ሕይወት እንጂ ብዙሃኑ በ21ኛው ክ/ዘመን ውስጥ የሚኖር በማይመስል መልኩ የሀገሩ ሀብት እየተዘረፈ ከድህነት ወደ ድህነት እየወረደ ለመሆኑን ይህንን እንደወረደ የተቀረፀ ፊልም መመልከት ነው።ፊልሙ ሌሎች ከተሞች እና የገጠር አካባቢዎችም በመጠኑ ይዳስሳል፣ ፖሊሶች በሕዝቡ ላይ የሚያደርሱትን ግፍ ከፎቅ ላይ በተነሳ ፊልም ያጋልጣል። በእዚህ ሕዝብ ስም ብድር ተወስዷል።ሕዝቡ ለመኖር ይታትራል።ጥቂቶች በስሙ ተበድረው በቢልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ዘርፈው በቅንጦት ይኖራሉ።ነፃነት ማለት ይህንን ድሃ ሕዝብ ነፃ ማውጣት የሀገሪቱን ሀብት እንደአቅሙ እንዲካፈል ማድረግ እና ከመከራ ኑሮ ማውጣትም ነው።
ምንጭ (Source) : - paul carton Published on Sep 1, 2016
ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com
No comments:
Post a Comment