Friday, October 21, 2016

ህዝቡ ዲሽ ሊነቅሉ የሚመጡ የሕወሓት ወታደሮችን የመምታት ሙሉ መብት አለው።ንብረትን መከላከል የሞራል ግዴታ ነው!መረጃ የማግኘት መብት ዓለም አቀፍ ድንጋጌ ነው።

ጉዳያችን
ጥቅምት 12፣2009 ዓም
====================================
ዲሽ (የሳተላይት መቀበያ ሳህን)  የዓለም አቀፍ ዜናዎችን ከዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች የምንከታተልበት የመገናኛ መሳርያ ነው።ሰሞኑን የሕወሓት ቅልብ የአጋዚ ሰራዊት እና ሚሊሻ በእየቤቱ እየገባ ዲሽ መንቀል እና መስበር መጀመሩ ተሰምቷል።የቴሌቭዥን ቻናል መቀበያ ዲሽ አንድ ኢትዮጵያዊ ለፍቶ ካገኘው ንብረት ውስጥ ዋጋ አውጥቶ የገዛው የግል ንብረቱ ነው።ዲሽ መስቀል እና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን መከታተል ወንጀል አይደለም።

ዲሽ ሊነቅል የሚመጣ ማናቸውም ፖሊስ ሆነ ወታደር፣ካድሬ  መመታት አለበት።ሕዝብ ንብረቱን የመከላከል ሙሉ መብት አለው።በእዚህ ጉዳይ ላይ መወላወል አይገባም።ኢትዮጵያዊ ሁሉ ቤቱ መጥቶ ንብረቱን ሊሰብር የመጣን ማንኛውንም ሰው በግልም ሆነ በቡድን ማጥቃት  የሞራል ልዕልና ነው።ሃገርን መከላከል የግል ንብረትን ከመጠበቅ ይጀምራል።መረጃ የማግኘት ሙሉ መብት እንዳለህ/ እንዳለሽ ማወቅ አለብህ።መረጃ የማግኘት መብት  በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደነገገ መብትም ነው። በእዚህ ጉዳይ አክትቪስቶች ህዝብን ማንቃት አለባቸው።የእዚህ አይነቱን ተግባር ሕዝብ አምርሮ እንዲታገል አለማድረግ ባርነትን እንዲለምድ ማበረታታት ነው።ስለሆነም በእዚህ ጉዳይ ላይ ሕዝብ አምርሮ ንብረቱን እንዲከላከል ማንቃት ከመገናኛ ብዙሃንም ብዙ ይጠበቃል።


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...