Wednesday, June 3, 2015

ጥንታዊ በግዕዝ የተፃፉ የብራና መፃሕፍትን ጨምሮ በርካታ ጥንታዊ መፃህፍት በሶርያ በረሃ በ''አይኤስ ኤስ'' ከመቃጠል ተረፉ (ቪድዮ)

ከሶርያ ዋና ከተማ ከደማስቆ ሰሜን  200 ኪሜትር እርቀት የምትገኘው የምድረ በዳ ከተማ በግዕዝ የተፃፉ ጥንታዊ የብራና ፅሁፎችን ጨምሮ  በግመል እና አህያ ተጭነው ለመትረፍ ቻሉ።በፊልሙ 3 ደቂቃ ከ22 ሰከንድ ጀምሮ ከሚታዩት መፃፍት ውስጥ በግዕዝ የተፃፈ አነስተኛ መፅሐፍ ይታያል።
የፈረንሳይ ቴሌቭዥን ''ፍራንስ 24'' ትናንት ግንቦት 25/2007 ዓም በለቀቀው ቪድዮ ቄስ ናጅብ ሚካኤል የተሰኙ አባት ቅርሶቹን ዲጂታል ፎቶ በማንሳት፣እራሳቸው በአህያ እና በግመል በማመላለስ እንዲሁም በስደተኛው ሕዝብ ሻንጣ ውስጥ በመጨመር መፃህፍቱ ለትውልድ እንዲተርፉ አድርገዋል።የግዕዝ መፅሐፉ መታየት ግን  ጥንት አባቶቻችን ለመንፈሳዊ አገልግሎት ያልረገጡት መሬት እንዳልነበር ያሳያል።


የ''ፍራንስ 24'' ቴሌቭዥን  ቪድዮ ከእዚህ በታች ይመለከቱ   -



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

ወቅታዊው እና መጪው የኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ምጣኔሃብታዊ እና ማኅበራዊ ሁኔታ በሶስት ርዕሶች ማጠቃለል ይቻላል።

  ፎቶ ፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2017 ዓም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ መትከል ብሔራዊ ዘመቻ ሲከፍቱ። ========= ጉዳያችን ምጥን ======== በእዚህ ጽሑፍ ስር ሶስት ምጥን ርዕሶች ያገኛሉ። እነርሱም  አ...