Wednesday, June 10, 2015

ጣልያን እጥፍ ሲል እንደ ሮማ መንገዶች ነው። ይህ ጣልያን ነው (የጉዳያችን ምጥን)


 ከእዚህ በላይ ያለው ፎቶ በአንድ ወቅት ጠላት የነበሩ ሀገሮች መሪዎች ፕሬዝዳንት ኦባማ እና  የጀርመን ቻንስለር አንግሌ መራክልከሶስት ቀናት በፊት በቡድን 7 ስብሰባ ወቅት በእረፍት ሰዓት  ሲነጋገሩ ያሳያል።
  Photo -huffingtonpost.co.uk 

የጣልያኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ማተዎ ረንዚ ( Matteo Renzi) በሶስት ቀናት ልዩነት ውስጥ ብዙ ሥራ እንደሚሰሩ አስመሰከሩ።በሩስያ ላይ እቀባ ካደረጉት ከቡድን ሰባት አባላት ጋር ስብሰባ ተቀምጠው ሩስያ ስትታማ እና ምናልባትም ሲያሟት ከርመው  ዛሬ ዘወር ብለው የሩስያውን ፕሬዝዳንት ፑቲንን  በሀገራቸው እያስተናገዱ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፑቲን ጋር በጋራ በጣልያኗ ከተማ ሚላኖ በሰጡት መግለጫ ''ሩስያ ለዓለም ጠቃሚ ሀገር መሆኗን እና ሽብርተኝነትን ጨምሮ ብዙ የጋራ አጀንዳ ከአውሮፓ ጋር ያላት መሆኑን''ሲያብራሩ ፑቲን እራሳቸውን ወደላይ እና ወደታች እያደረጉ አድንቀውላቸዋል።ይህ ጣልያን ነው።ጣልያን እጥፍ ሲል እንደ ሮማ መንገዶች ነው።ለነገሩ በሩስያ ላይ የተደረገው እቀባ ለአውሮፓ ብዙም እንዳልተመቸው በብርቱ ይታመናል።

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ሰኔ 3/2007 ዓም (ጁን 10/2015)

No comments:

''ሙዝ አትብላ! ጦጣዎች ከጫካ ሊመጡ ይችላሉ።'' ዓይነቱ የጀዋር ጊዜው ያለፈበት ትንተና በኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ላይ።

ቀይ ባሕር ዛሬ በዩቱብ አገኘን ብላችሁ በኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ላይ የምትሳለቁ የዘመናችን ባንዳዎች ግዴላችሁም ጊዜ እና ትውልድ ይፈርዳል! እናንተን ብቻ ሳይሆን ልጆቻችሁም ''አባታቸው በዩቱብ ኢትዮጵያ ...