ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, October 10, 2012

አጭር ምክር ብጤ -''አሜሪካ የ ውጭ ፖሊሲሽን ቀይሪ'' ብለው የምርጫ ካርድ ለመዘዙት


አጭር ምክር ብጤ
በቅርቡ በሚደረገው አሜሪካ ምርጫ ሳቢያ ትውልደ ኢትዮጵያውያን-አሜሪካውያን አሜሪካ ውጭ ፖሊሲ ኢትዮጵያ ካለው ሰብአዊ መብት አያያዝ ጋር በተያያዘ እንዲቀየር ለሚያሳስቡ ወገኖች አንድ የዘነጉት ነገር ያለ መሰለኝ።

''አሁን እየተባለ ያለው አሜሪካ የውጭ ፖሊሲሽን ቀይሪ ነው።'' እንደዚህ አይነት ''ቀይሪ '' ከሚል መልክት ይልቅ ቅርቡ አሜሪካም ይደረጋል የሚባለው ኢትዮጵያውያን ስብሰባ አቀራረብ መልክ ቢኖረው ጥሩ ነው። አንዲት ሀገር ውጭ ፖሊሲዋ የሚመሰረተው ጋራ ጥቅም ላይ ነው። ጥቅሟ ትንሽ ነገር ከተሸረፈች ምንም ነገር ላይ ለመገኘት 'ሞራል' የሚለው ጉዳይ ዜና አውታሮች ዘንድ እስካልተጋለጠ ድረስ ብዙም ችግር አደለም ብሎ ማሰብ አለሙ እየለመደው ነው።

በመሆኑም ስብሰባው ጥናት ፅሁፎችን ታዋቂ ፖሊሲ አጥኝዎችን እና ፖሊሲው ሲቀየር   አሜሪካ ዘለቂታ ጥቅም አንፃር እንጂ ሰብአዊ መብት ስለተጣሰ ብቻ አሜሪካንን ፖሊሲሽን ቀይሪ የሚል አቀራረብ '' ልብ ባይነካስ ?'' ብሎ ማሰብ ተገቢ ነው።እዚህ ላይ ከ እዚህ ቀደም ብዙ ሰልፍ ሲደረጉ መክረማቸውን ልብ በሉልኝ። አሁን ወደ አውነታው አለም መምጣት ያለብን ይመስለኛል።የ እዚህ አይነት ሰበአዊ መብትን  እና ምርጫ ካርድን ብቻ በመምዘዝ የሚደረግ ተፅኖ ዲፕሎማሲያው መልስ ያላለፈ ምላሽ ማለትም ''ጉዳዩን እናየዋለን '' አይነት ምላሽ እና ምርጫው እስክሳካ ድረስ መንከባከብን ብቻ ማስከተሉ አይቀርም ።በ መሆኑም ዋናው ነገር ፖሊሲዋን መከለስ ያለባት በልመና ሳይሆን እራሷ ስትል ዘለቄታ ጥቅም አንፃር መሆኑን ማሳመኑ ላይ ነው ቁልፉ ተግባር ያለው

ይህ ደግሞ አስደንጋጭ ስታትስቲክስ የያዙ ማስረጃዎች፣ ጥናት ፅሁፎች እና ታዋቂ ተናጋሪዎችን ማቅረብ እና አሜሪካ የውጭ ፖሊሲዋን ተጠየቀው መንገድ ካልቀይረች የሚደርስባትን ክስረት የሚያመላክት ማስረጃ ፈልጎ ማቅረብን ሁሉ ይጠይቃል። ይህ እንግዲህ አሜሪካ ፖሊስ አውጭዎችም ዘንድ ሁሉ ክርክር የሚያስነሳ አዲስ ዘገባን ሁሉ ይዞ መውጣትን ይጠይቃል። ስብሰባው ጥሪ ጀምሮ መንፈሱ ሁሉ '' አሜሪካ ዘለቂታ ውጭ ፖሊሲ እንሰራለን! '' የሚል መንፈስ ያለው አሜሪካ ተቆርቃርነት የሚያሳይ መንፈስም ማዘል አአለበት። አሜሪካዊ ኢትዮጵያውያን ለሆኑቱ ማለት ነው። ይህ ወደ ገንቢ ተፅኖ ይመራል። ቅኝቱም መሆን ያለበት እንዲህ ይመስለኛል።

እዚህ በዘለለ ግን ምርጫ ካርድ እና ሰብአዊ መብት ጉዳይ በማንሳት ብቻ አሜሪካ የሚያስከትለውን ጥቅም ጉዳት በደንብ በማስረጃ ሳያመላክቱ የሚደረጉ ስብሰባዎች እቅድ አፈፃፀም ብቻ ነው የሚሆኑት። ከተሳሳትኩ አርሙኝ።


አበቃሁ
ጌታቸው
 
ኦስሎ 

1 comment:

Anonymous said...

Thank you for sharing ideas. Hule yemnchohew yhn new here in DC.