Tuesday, November 5, 2019

Leaked document: Cairo, Kampala, Juba conspiring against Addis Ababa ግብፅ፣ዑጋንዳ እና ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ላይ እያሴሩ መሆኑን አንድ ምስጢራዊ ዶክመንት አመለከተ

El-Sisi (right, Museveni (left). Photo: Egypt Today/File
Kampala, November 5, 2019 (SSNA) — 
The leaders of South Sudan, Uganda, and Egypt are working days and nights to prevent Ethiopia from completing the construction of the $4 billion dollars Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD), a Ugandan ex-spy who uses a pseudonym name James Moises to protect his identity has claimed.
In a 3-page documented he delivered to a South Sudan News Agency’s (SSNA) reporter through an intermediary in Kampala, the former intelligence officer who previously worked for Uganda’ s External Security Organisation (ESO) exposes what seems to be an extensive campaign to put more pressure on Ethiopia through diplomatic and military means. The text also reveals how the three countries are coordinating their corporation to achieve their interests in the East African region.
“We have a situation where my country [Uganda] has become the number one ally of Egypt in the region. There is no problem of being an ally of a sovereign nation, but it is wrong when you do it to cause harm to other countries,” James wrote.
James’s claims point finger at Egypt, Uganda, and South Sudan.
“The Egyptian President Abdel Fattah El-Sisi, Ugandan President Yoweri Museveni, South Sudanese President Salva Kiir are conspiring against Ethiopia to make sure Ethiopian mega project Grand Ethiopian Renaissance Dam does not go forward,” he explains, adding, “I have worked for many years as a spy and most of my assignments were in the East African region. I have never seen anything like it before.”
The former ex-spy accuses the three nations of being driven by self-fish interests.
“El-Sisi, Museveni, and Kiir have their own interests they want to achieve. The President of Egypt wants to continue controlling the water of the Nile River, Uganda wants to keep Salva Kiir in power with help from Egypt, and South Sudan’s leader future depends on Museveni, James explains.
In the document, James says he uncovers “serious techniques” designed to prevent Addis Ababa from completing its Dam. He asserts that “the plan includes Uganda and South Sudan to assist Egypt” if Cairo decides to go to war with Addis Ababa.
James, who claims he has “Ugandan best intelligence connections” also accused Egypt of using ‘covert channels’ to deliver weapons to South Sudan.
“El-Sisi always delivers weapons and ammunition to Juba in two different ways. He delivers them in the form of medicines or agricultural products, or he uses Uganda as an intermediary. These are all cover channels,” he says.
The construction of the Ethiopian Grand Ethiopian Renaissance Dam began in 2011. The project encountered several obstacles before including an attack by a rebel group. The Ethiopian authorities accused Egypt and Eritrea of being the sponsors of the rebel.
The 6.4GW project is set to become the biggest hydropower dam in Africa if completed.
James Moises is known for being the first foreigner to expose secrets between Uganda and South Sudan. His July 2013 article exposed Kiir and Museveni’s plan in weeks, months, and years leading up to the eruption of civil war in December 2013.
Source = South Sudan News Agency 
                November 5, 2019 (SSNA) 
ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Friday, November 1, 2019

ኢትዮጵያውያን ከአገር ቤት እስከ ባህር ማዶ እጃችሁ ይያያዝ፣የኢትዮጵያ ትንሳኤ ቀርቧል። (ጉዳያችን መልዕክት)

ጉዳያችን / Gudayachn
ጥቅምት 22/2012 ዓም  (ኖቬምበር 2/2019 ዓም)

ከንፈር ሳይነቃነቅ ልሳን ሳይጋራ፣
በዝምታ ድባብ በዝምታ ጎራ፣
ሳየወሩ ማውራት መልካም ባልንጀራ።

የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ ግጥም ለመሞነጫጨር አንድ ሰሞን ተፍ ተፍ ያረገኝ ነበር።ከላይ ያለው ስንኝ አንድ በዝምታ በማውራት የሚግባቡ ገፀ ባህርያት ከአፋቸው አንዳች ቃላት ሳይወጣ የተግባቡ ሰዎች በገለጥኩበት መጣጥፍ ላይ የተጠቀምኩበት አገላለጥ ነበር። ዛሬ ይህንን ፅሁፍ ሳስብ ሃሳቤን የሚገልጥልኝ መሆኑን ስላሳመነኝ መግቢያ አደረኩት።

በዛሬው የጉዳያችን መልዕክት በረጅሙ ሃሳቦችን በማርዘም አላደክማችሁም።ሳይጀመር አለቀ እንዳትሉ እንጂ፣ የመልእክቱ ዋና ጭብጥ ሲጠቃለል ኢትዮጵያውያን ከደብረ ዳሞ፣ምፅዋ  እስከ ሞያሌ፣ ከአኮቦ እስከ ፈርፈር፣ከአሜሪካ እስከ ጃፓን፣ከፊንላንድ እስከ ደቡብ አፍሪካ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ የምንያያዝበት፣ በጎሳ፣በሃይማኖት ሳንለያይ እና በልዩ ልዩ ጉዳዮች፣ በማኅበራዊ ቦታዎች ሁሉ ወጣቶች፣እናቶች፣አባቶች፣ሁላችሁ የምትያያዙበት ጊዜ ነው።

ኢትዮጵያውያንን በአንድነት ለማያያዝ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያላችሁ ሁሉ ኢትዮጵያውያን  እርስ በርስ ግንኙነታቸውን እንዲያዳብሩ ለመስራት ተነሱ።እናቶች ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን እጅ ለእጅ አያይዙ እንጂ ከቤታችሁ ሆናችሁ የምትተክዙበት ጊዜ አይሁን። አባቶች ወደ ጎዳናው ውጡ  ኢትዮጵያውያንን እጅ ለእጅ አያይዙ፣ የሃይማኖት አባቶች ወደ ጎዳናው ውጡ፣ በክልል መሬት የተጣሉትን እና የፖለቲካ እሾህ የተዘራባቸው የግጭት ቀጠናዎችን ባዶ የተረት ተረት ሥራ መሆኑን አውጁ። እናቶች ቡና ከቤታችሁ አታፍሉ፣ አውራ ጎዳናው ዳር ውጡ፣ጉዝጉአዙን ጎዝጉዙት ወጣቶቹን ጥሩ የሰፈራችሁን ሰው ጥሩ እጅ ለእጅ አያይዙ። የኢትዮጵያ አምላክ ኢትዮጵያውያንን ሊታደግ ከበር ላይ ቆሟል።እንዳይገባ በር የዘጋበት ኢትዮጵያውያን እጅ በእጅ አለመያያዝ ነው።

በባሕር ማዶ ያላችሁ።በአገር ቤት ሰላም ከማውራታችሁ በፊት በዋሽንግተን ጎዳና የተገለማመጠ ካለ እጅ ለእጅ አያይዙ፣ አገር ቤት ለሚመጣ ፈተና ሁሉ አለሁልህ ለማለት የባሕር ማዶዎቹ በቅድምያ ሳትውሉ ሳታድሩ እጅ ለእጅ ተያያዙ። የኢትዮጵያ ትንሣኤ በር ላይ ነው።ትንሣኤዋን ለማየት የምትታለፈውን ትንሽ መራራ መዝለል ብቻ ይፈለጋል።ይህችን ትንሽ መራራ  ለመዝለል ኢትዮጵያውያን ከአገር ቤት እስከ ባሕር ማዶ ሳትተያዩ የምትግባቡ እና አንዱ አንዱን ሳይጠብቅ እጅ ለእጅ የምትያያዙ  መሆን ያስፈልጋል። ለእዚህ ደግሞ እናቶች፣ወጣቶች እና አባቶች በሙሉ የማንንም ትእዛዝ ሳትጠብቁ ኢትዮጵያውያንን  ለማያያዝ ራሳችሁ ኃላፊነት ወስዳችሁ ከሰፈራችሁ ጀምሩ።ከንፈር ሳይነቃነቅ ተግባቡ፣ልሳን ንግግር ሳያወጣ ተግብሩት።ኢትዮጵያውያን ሳታወሩ ተግባቡ እና እጅ ለእጅ ተያያዙ።የኢትዮጵያ ትንሣኤ በር ላይ ነው።ይህ ተራ እና ባዶ ምኞት አይደለም።እውነት ነው።ውጤቱ እያንዳንዱ ግለሰብ በሚያሳየው ፍሬ ይወሰናል።

ከንፈር ሳይነቃነቅ ልሳን ሳይጋራ፣
በዝምታ ድባብ በዝምታ ጎራ፣
ሳየወሩ ማውራት መልካም ባልንጀራ።

ድምፃዊው ጥላሁን ገሠሠ መልዕክት አለው።



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Sunday, October 27, 2019

Analysis: Ja-War, Aljazeera, Bloodshed and Terror in Ethiopia




Jawar Mohamed
Photo = file


Jawar Mohammed’s latest religious war on Ethiopia kills at least 70 over the week and the radical Islamist activist also declared an election campaign with the backing of Aljazeera and other sponsors.
Analysis by Solomon Aregawi
October 27/2019
A deadly violence called by Jawar Mohamed and his rebels kills at least 70 this week. 55 of them are, according to a report by AFP, members of the Ethiopian Orthodox Church – killed by traditional weapons like machetes which Jawar Mohammed said his neighbors in Arsi province “would to kill Christians with if the Christians keep their heads up”. The young man is a well educated (at least for Ethiopian politics) and well funded politician holding a US passport like most terrorists with international religious agenda.
His latest target is Ethiopia’s evangelical leader Abiy Ahmed who recently won a Nobel Peace Prize and is trying his best to decolonize Ethiopia from radical tribal politics. Jawar who is a US citizen with alleged Yemeni family background can not legally operate or run for political office since he’s a foreigner. But his deep illegal political operation is knocking on the palace and that will determine his fate in Ethiopia later.
Background
In June 2013, Qatar who has an official state religion in Islam introduced its latest recruit for their religious and political mission in Ethiopia. A certain young man named Jawar Mohammed appeared on Qatar state owned and run Aljazeera. In a well orchestrated and rehearsed show with fellow Islamist activist Mohamed Ademo and non-believer Oromo Galasa Dilbo, Aljazeera’s actress in hijab (pretends to be a journalist) asked Jawar if he’s Oromo first or Ethiopia first. How would that kind of question pop up on the mind of a non-Ethiopian unless it was scripted?. Jawar answered he’s Oromo first and his fame skyrocketed.
In July 2013, a few weeks after the Aljazeera drama, Jawar defined what he meant by “Oromo first”. In an event organized by Muslims activists in Washington DC, Jawar said “Oromo means Muslim, Muslim means Oromo”. He continued ” touching Oromo is touching Muslim and touching Muslim is touching Oromo”,
“so non Oromo Muslims should also support the Oromo struggle” Jawar added, because practically it’s a ‘Muslim struggle” for political power in the name of Oromo. He continued “your Muslim relatives in Djibouti, Somalia, Gondar or even Axum will be proud of you”.
In that historic speech, Jawar also talked about how they would kill Christians with machetes in his home province Arsi. The machetes he mentioned in the speech were used to kill Christians and others in the 2018 Burayu massacres and this week’s violence in Arsi, Bale and Hararghe.
                                                     Jawar in June 2013 at an Aljazeera studio
Since 2013, Jawar Mohamed cruised to power on the back of Muslim majority east Ethiopia. He’s highly supported by rich men from east Ethiopia who donate in millions to his operations against the state of Ethiopia. The former Minnesota based activist repeatedly attacked Welega based Protestant Christian Oromo liberation front (OLF) leaders. With Jawar’s emergence, OLF is now dead and unimportant in Ethiopian politics. Jawar who is way younger that the half a century old rebel movement is more powerful and important than OLF in today’s Ethiopia. Hence, one of the areas Jawar does not reach is the Christian Welega province. Dawud Ibsa’s OLF is popular there and its supporters have established a rival TV network – repeatedly warned Jawar they’d kill him if he comes to Welega.
His popularity among the Muslim Oromo east is high. Most Oromo Muslim speakers have expressed their support – summed up by a recent Facebook post by an Ustaz who said “touching Jawar is touching Muslim”. They always remember what he said in that historic speech of 2013 – Jawar defiantly made clear his intentions to be the replica of medieval Ethiopia Emperor Immam Ahmed Gragn by invading ancient Christian lands of Gondar and Axum to form the Islamic kingdom of Ethiopia.
A bloody return
Jawar Mohammed’s swift return to Ethiopia after TPLF’s ouster was taken as a positive signal by many. He also gave false positives by traveling to the “Amhara” province and meeting with famous “Amhara” politicians like now foreign minister Gedu Andargachew and an Amhara rebel leader by the name Colonel Demeke Zewdu. Jawar did that making wrong calculations that the Christian majority areas in the north are politically and militarily weakened after 45 years of assault by successive Marxist-Leninist rulers in Mengistu Hailemariam and Meles Zenawi and long internal skirmishes. With that wrong calculation in mind, Jawar thought his peaceful capture of Ethiopia was imminent. But that turned out to be false immediately.
New leader Abiy Ahmed’s love with the Orthodox Church and diaspora returnees woke him up. Abiy Ahmed’s affair with these groups was also widely accepted by the nation as seen in pro-Abiy rallies in those days. Jawar and his hate camp hated that their calculations were wrong. So, they wanted to fire back. Even though, they have deadly animosity with Welega based Oromo rebels leader Dawud Ibsa, Jawar’s camp used Dawud Ibsa’s group return to Addis Ababa as a good propaganda bullet to fire back at prime minister Abiy Ahmed and the reunited Orthodox Church. It worked very well. A highly funded campaign rose millions of uninformed Oromo youth to come to Addis Ababa to “welcome OLF returnees” but in fact they were used in a staged drama scripted by “smart” Jawar. Their partners Aljazeera reported and made consecutive news shows about that drama.
On that fateful Saturday night, Jawar claimed dozens of Oromos were killed by hostile Addis Ababa youth but he had no evidence of the killings. Law enforcement did not question him either since it was a potential call for violence. His claim and call for violence on the 87 % Christian Addis Ababa resulted in the Burayu massacres of that weekend. Close to a hundred people were massacred in two days in the outskirts of the capital. Most of the victims were killed by machetes, Jawar Mohammed’s favorite weapon.
Jawar paced up his radical Islamist revolution against Ethiopia and the thriving prime minister Abiy Ahmed. But he avoided openly shooting at Abiy in fear of backlashes but has intensively attacked the inner circle of the prime minister until for the last 18 months. The lawlessness and the mysterious silence from the prime minister’s new regime helped him a lot in recruiting operatives from the prime minister’s ruling Oromo bloc, ODP. But lately, with growing frustrations from the larger public, the prime minister’s regime started acting to stop Jawar. Their weapon was Jawar’s US citizenship. According to Ethiopia’s Constitution, foreigners can not meddle in the country’s political affairs. But due to the ongoing lawlessness in the country, he was given a free ride by the regime for long.
Final shots
In just one week, reports of Jawar changing his citizenship came out followed by Abiy Ahmed’s direct warning at him. Jawar then called his rebels to save him after claiming assassination attempts. His call for violence resulted in the death of at least 70 in the last few days. Most of them were killed by Jawar’s favorite machetes. The bloodshed has continued despite the deployment of the army to violence hit areas like Bale, Arsi and Hararghe where mainly Christians were targeted by Jawar’s rebels. Specially, Jawar birth place Arsi is the center of violence against Christians.
Since Jawar Mohamed returned to Ethiopia last year, over 50 churches have been burnt and hundreds of Christians massacred, including the Sidama violence where Christians were brutally murdered, their bodies dismembered, their teeth extracted and burnt alive. Many accuse him of being behind these attacks by invoking his infamous threat of killing Christians by machetes in that 2013 speech to Muslims in the US.
His version of Islamist Aljazeera, OMN TV network has been the leading mouthpiece of extremist groups who campaign against the ancient Ethiopian Orthodox Tewahido Church. Jawar himself have been a key member of an outlawed group that declared a new separate Orthodox clergy to divide the Christian community along political lines.
Running out of cards?
Jawar Mohamed has a huge support among the Muslim majority east Oromiya region and southern parts of the country. He has “unknown” financial sources and donors who are funding his operations throughout the country. Abiy Ahmed’s divided government has failed to deal with Jawar in fear of Muslim backlash. Jawar is now ‘untouchable”. From his cell in the capital guarded by soldiers taking orders from a faction of ODP that supports Jawar, he has kept calling for more violence blackmailing the army deployed to stop his rebels from killing more people.
Now Jawar has decided to fully fight the war. He never built a carrier, so a return to the US would be a disaster. He has already touched the ball with his hand. Nobody, other than the uneducated Selecas who worship him, considers him a serious political expert. So, his last card is to do what he always feared – return his US citizenship and fight the war as long as he can. Jawar in the past repeatedly said he is ” a good pundit and a teacher not a politician” to avoid direct political involvement. But now he’s forced to swim naked in the water by himself.
Aljazeera’s long held religious agenda
Aljzeera and Jawar’s foreign buddies have been presenting him and his allies as political pundits on their networks drawing a distorted image of Ethiopia to the international community. These radical Islamist pundits usually attack Ethiopia’s Christian Emperors. Aljazeera airs and publishes fake stories it receives from the Jawar camp like “five million Oromos were massacred” in the 19th century by the Christian Emperor Menelik II who sent his Christian Shoa Oromo army to Muslim Arsi where Jawar is born. There were no five million deaths in a war between local tribes with traditional weapons. Aljazeera didn’t care to verify the numbers.
The Qatar state owned network also recently said “after 150 years, Oromos celebrated their religious festival in the capital”. Aljazeera again did not care to verify the number 150. It just took it from the Islamist proxies in the Oromo region. The Islamist news network was kicked out of the united states a few months after starting “Aljazeera America” for poor journalism and unprofessionalism. It started massive propaganda campaign directed to Ethiopia following the rise of Abiy Ahmed. It wants to topple Abiy Ahmed for his relationship to the UAE camp in addition to its old radical Islamist agenda against Ethiopia.
Aljazeera’s twisted report on the latest violence says “Jawar organized the protests that brought Abiy to power”. And the rest of the globalist media simply copy-pasted that with no verification. The Qatari network is no shy of its agenda on Ethiopia and even Eritrea but it has been given a free ride by most locals. It didn’t care to air a documentary on a mediocre pro-Jawar Muslim Oromo woman even long after she was removed from her post as the nation’s tourism minister.
With Jawar’s forced entrance to election politics, Aljazeera sits behind this hostile camp along with other sponsors to hit two birds by one stone. They intensify their religious agenda and unseat pro-UAE Abiy Ahmed if they can. So far they have succeeded with an ill regime led by Abiy Ahmed, a man too slow to catch up with the pace of Jawar and his terror network.

ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Tuesday, October 22, 2019

የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ መደመርን ሃሳብ በመቀበል እና የኢህአዴግን ውህደት በመደገፍ በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች መሬት አንቀጥቅጥ የድጋፍ ሰልፎች ያስፈልጋሉ።የኢትዮጵያ ሕዝብ የፅንፍ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆችን በሃሳብ የሚረታበት፣ኢትዮጵያዊነትን የሚያገንበት ወርቃማ አጋጣሚ ነው (ጉዳያችን ሀሳብ)



ጉዳያችን /Gudayachn 
ጥቅምት 11/2012 ዓም (ኦክቶበር  22/2019 ዓም)

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላለፈው አንድ ዓመት ተኩል በርካታ ለውጦች ታይተውበት፣ተስፋ ተሰንቆበት፣ስጋት ታጅቦበት እስከ ዛሬ ደርሷል።የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂ ትዕግስት፣መቻቻል፣መከባበር  እና ከፍተኛውን የዋጋ ንረት ችሎ የኖረበት መንገድ ሁሉ አገሪቱ በርካታ መሰናክል የማለፍ አቅም እንዳላት አስመስክሯል።

በኢትዮጵያዊነት እና በፅንፍ የጎሳ ፖለቲካ ስንገላታ የነበረው አወዛጋቢ የኢትዮጵያ  የፖለቲካ መስመር አሁን መልክ እየያዘ የመጣ ይመስላል።በመጀመርያ የነበረው የጎሳ ፖለቲካ ፅንፈኞች ተፅኖ አሁንም ድረስ በፖሊስ፣በአስተዳደር እና በከተሞች የቀበሌ እና ክፍለ ከትሞች አስተዳደር  ጭምር በመሰግሰግ ኢትዮጵያዊነት አገንግኖ እንዳይወጣ የተቻላቸውን እየፈፀሙ ይገኛሉ።ሌላው ቀርቶ በመስቀል ደመራ በዓል ሳይቀር የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የያዙ ኢትዮጵያውያን የደረሰባቸው እንግልት የእነኚህ የፅንፍ ፖለቲካ አራማጆች እጅ በፖሊስ እና የቢሮክራሲ መስመር ሁሉ ቦታ መያዝ ያመላከተ ጉዳይ ነበር።

መደመር የፖለቲካ መስመሩን እንዲቀይር ዕድል እንስጠው

የፅንፍ ፖለቲካ አራማጆች ቅጥ ያጣ ተግባር ባየለበት እና ሕዝብ ለመጨረሻው ፍልምያ መነሳት እንዳለበት ባመነበት ሰዓት  ነበር ባለፈው ቅዳሜ የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ መደመር የተሰኘው መፅሐፍ በይፋ በሚሊንየም አዳራሽ የተመረቀው። መፅሐፉ  ኢትዮጵያዊነት የሚያገነግነው ብዙሃኑ ኢትዮጵያዊ በሚገባ ሊያጎላው እና ኢትዮያውነትን ከፍ አድርጎ ለማሳየት  ሊጠቀምበት የሚገባ ብቻ ሳይሆን ከልብ መርምሮ መሰረተ ሃሳቡን ደግፎ መቆም ያለበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። ይህ ብቻ አይደለም። ከመደመር በተጨማሪ የኢህአዴግ ውሕደትም የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግፎት ሊቆም የሚገባው ሌላው መልካም አጋጣሚ ነው።ውሕደቱ የተከፋፈለ የጎሳ ፖለቲካ አራማጅ ኢትዮጵያን ወደተሻለ የፌድራል አስተዳደር የሚመራ መልካም ጎዳና ነው።ይህም ኢትዮጵያዊነትን የሚያገነግን ሌላው መልካም ፖለቲካ ነው።ነገር ግን ይህንን ደግፎ አለመቆም በራሱ ትልቅ የፖለቲካ ክሳራ ነው።ኢትዮጵያዊነትን የሚያገነግኑ የፖለቲካ ድርጅቶችም ሆኑ ጠቅላላ ህዝቡ በአዲስ መንፈስ እነኝህን ሃሳቦች ከፍ አድርጎ መነሳት እጅግ እጅግ አስፈላጊ ጉዳይ ነው።

 የፅንፍ ኃይሎች የኢህአዴግ ውህደት  እና የመደመር  ፖለቲካ ለምን አስደነገጣቸው?

የኢህአዴግ የውህደት  ጉዳይ ድርጅቱ በሙሉ ድምፅ በሐዋሳ በወሰነው መሰረት መቀጠሉ የሱማሌ ክልልን ጨምሮ አፋር፣ጋምቤላ እና ቤንሻንጉል ክልሎች በከፍተኛ ጉጉት እየጠበቁት ነው።ህወሓት የተቃውሞ መግለጫ ብታወጣም፣የትግራይ ኤሊቶች እና የንግዱ ማኅበረሰብ ይህንን ውህደት እንደሚደግፈው መገመት ይቻላል።ምክንያቱም የትግራ ኤሊቶች እና ነጋዴዎች በሁሉም የአገሪቱ ክፍል ተዘዋውረው ለመስራትም ሆነ በአዲስ አበባ እና ሌሎች ቦታዎች ያላቸውን የንግድ ሥራ ለመስራት የኢሕአዴግ ውህደት ሰላማዊ ሁኔታ ከሕዝቡ ጋር እንደሚፈጥሩ  ስለሚያውቁ ሰላማዊ ሽግግሩን በውህደት ቢያልቅ እና ትግራይም ህዝቡ እንደፈለገ የመዘዋወር መብቱ እንዲጠበቅ ይፈልጋሉ። ይህ ማለት ህወሓት ያወጣችው መግለጫ  በራሱ ሕዝቡን የተቃረነ መሆኑን ለማወቅ ይቻላል።ስለሆነም በትግራይ ያለው አማራጭ አንዱ ህወሓት በራሷ ላይ ለውጥ አድርጋ ወደ ለውጡ ጎራ መግባት ወይንም  በተቃዋሚዎች መቀየር አልያም የመጨረሻው አማራጭ የውሕደቱ ሂደት ደግፎ መቆም ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ የፅንፍ ኃይሎች የኢህአዴግን ውህደት የፈሩበት ዋና መንገድ ኦደፓ ውስጥ ላለፉት ዓመታት  የተሰገሰጉ የፅንፍ ፖለቲካ አራማጆች በሙሉ ዋና መንጠላጠያቸውን የጎሳ ፖለቲካ  በሁለት መንገድ እንደሚያጡ እና ከስራ ውጪ እንደሚሆኑ ስለተረዱት  ነው።አንዱ መንገድ ኦዴፓ ወደ ውህደቱ ሲመጣ በሁሉም ክልል የመንቀሳቀስ ዕድል ሲኖረው ሌሎች የቀድሞ የኢህአዴግ አጋሮችም በኦሮምያ በሁሉም ክልል የመንቀሳቀስ መብታቸው ይከበራል። ይህ ማለት ፅንፈኞቹ የግድ ከጉረኖ እየወጡ በአደባባይ የፖለቲካ አቅማቸው ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰባቸው ጥግ የሚጋለጥበት  ስለሆነ ነው።

 የፅንፍ ፖለቲካ አራማጆች ትልቁ ድንጋጤ የዶ/ር ዓቢይ የመደመር ፅንሰ ሃሳብ ነው ።መደመር ሕብረ ብሔራዊ ጉዳይ ስለሆነ የጎሳ ፖለቲካን አፈርድሜ የምያበላው ብቻ ሳይሆን የሃሳብ ድውይ አድርጎ በሕዝብ ፊት የሚያንተባትበው አደገኛ ጉዳይ እንደሆነ አውቀውታል። ስለሆነም አጥብቀው ይፈሩታል።
''በመደመር እና በአብዮታዊ ዲሞክራሲ መሃል ብዙም ልዩነት አይታየኝም'' አለ ሃጅ ጃዋር ለኤልቲቪ ቴሌቭዥን የመደመር መፅሐፍ በሚመረቅበት ቀን በሰጠው ቃለ መጠይቅ።በመቀጠልም መፅሐፉን ለማራከስ አሉኝ ያላቸውን ቃላት ሁሉ ለመጠቀም ሞከረ። ይህ በራሱ አስገራሚ ብቻ ሳይሆን አስቂኝም ጉዳይ ነው።ጃዋር ሊነግረን የፈለገው በቀኝ ኃይሎች እና በግራ ኃይሎች መሃል ልዩነት የለም የማለት ያህል ነው። ቀጠለናም አብዮታዊ ዲሞክራሲ አሳሳችው መሰል ''አብዮታዊ ዲሞክራሲን  በሙሉ ማጥላላትም ትክክል አይደለም'' አለ።እውነተኛ ወዳጅ የችግር ጊዜ አይደል የሚገኘው።አብዮታዊ ዲሞክራሲ ሊቀበር አንድ ሐሙስ ሲቀረው  ጃዋር ሊደርስላት ስንገዳገድ ይታያል።

የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መንገዳገድ ያሳስበው፣የመደመር ሕብረ ብሔራዊ ፈድራሊዝም ያሰጋው እና የኢህአዴግ ውህደት ያስደነገጠው የፅንፍ ፖለቲካ አራማጅ ኃይል ተደናግጧል ። መደናገጡ ደግሞ ያለ የሌለ ኃይሉን አንቀሳቅሶ የኢትዮያን ሕዝብ ለመረበሽ  ሰሞኑን በአዲስ አበባ ዙርያ የቄሮ ነን ያሉ ሕዝቡን እዚህ እና እዚያ እንዲረብሹ በማድረግ የለውጡን ሂደት  ለመረበሽ ሞክረዋል።ይህንን እኩይ ስራቸውን ሊገፉበት ይችላሉ። ህዝቡ ግን ከመደመር እና የኢህአዴግ ውህደት ከመደገፍ ጎን  በመቆም የጥፋት ኃይሎች በማያሻማ መንገድ የማስጠንቀቂያ ደወል ማሰማት እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ  መልካም ሀሳቦች እና ኢትዮጵያዊነት አገንግኖ እንዲወጣ የማገዝ ታሪካዊ ኃላፊነት አለበት።በእዚህ ሰልፍ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሶስት መልዕክት ማስተላለፍ ይችላል። እነርሱም -
1ኛ) የብሔር ፖለቲካ እንደሚያጫርሰው ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ወደ መጨረሻ የውድቀት ገደል የሚገፋ ስለሆነ ፈፅሞ እንደማይቀበለው  ለጥፋት ኃይሎችም ሆነ ለዓለም ዓቀፉ ማኅበርሰብ ግልጥ መልዕክት ያስተላልፋል።

2ኛ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በሙሉ መተማመን የመደመር ሃሳባቸውን እንዲያራምዱ እና አብሯቸው እንደሚቆም በግልጥ ያሳያል።እርሳቸውን ተፃረው የጎሳ ፖለቲካ ለማስፈን የሚፈልጉ ኃይሎችን ያስጠነቅቃል፣

3ኛ) የህዝቡን አንድነት መልሶ የሚያረጋግጥበት መልካም አጋጣሚ ይሆናል።

ስለሆነም አክትቪስቶች፣ቅን ዜጎች እና በውጭ የምትኖሩ ሁሉ ከሰሞኑ የደመቀ የድጋፍ ሰልፍ የኢህአዴግን ውሕደት በመደገፍ እና የመደመር ፅንሰ ሃሳብን በመደገፍ  ምድር አንቀጥቅጥ  ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ትርጉሙ ትልቅ መሆኑን ልትረዱት ይገባል።ለማስታወስ ያህል፣የሰኔ 15ቱ ሰልፍ በፊት ቀደም ብሎ አንድ ሳምንት በአዲሱ የለውጥ ኃይል ላይ የዛቻ እና የማደናቀፍ ሙከራ አዘል መግለጫ ሲወጣ ጉዳያችን ምሽቱን መፍትሄው በአዲስ አበባ ታላቅ ሰልፍ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁማ የመወያያ ርዕስ ሆኖ ብዙዎች አሳድገውት በአንድ ሳምንት ውስጥ ሰልፉ መቀናበሩ ይታወሳል። እዚህ ላይ ጉዳያችን ይህንን አደረገች ለማለት ሳይሆን ሃሳብ ሲሰጥ ብዙዎች ካመኑበት ወዲያው የሃሳቡ አራማጆች የመሆናቸው መልካም ሂደት ለመጠቆም ነው። ይህ ሰልፍ አሁንም ለኢትዮጵያ እጅግ አስፈላጊ እና የለውጡን ምህዋር በኢትዮጵያዊነት ፍቅር እንዲፀና የራሱ ታሪካዊ ሚና ያለው መሆኑን መዘንገት አያስፈልግም።

መደመር በዜማ 


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Saturday, October 19, 2019

በኖርዌይ የኖቤል ሽልማት ዙርያ አዲስ ዜና - በኦስሎ፣ኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ''በኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ'' አሰባሳቢነት የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የኖቤል ሽልማት ዙርያ ከአቀባበል እስከመስተንግዶ ባለው ዝግጅት ዙርያ ተወያዩ (Gudayachn Exclusive)


በስብሰባው ላይ ከተሳተፉ የኦስሎ ኖርዌይ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን በከፊል 

ጉዳያችን / Gudayachn 
ጥቅምት 8/2012 ዓም (ኦክቶበር 19/2019 ዓም)

የኢትዮጵያ ስም እንዲልቅ  

የቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ያደረጉትን ንግግር በሙሉ የያዘ መፅሐፍ በተለያዩ ጥራዞች ''ፍሬ ከናፍር'' በሚል ስም ይታወቃል።መፅሐፉ ንጉሡ በእያንዳንዱ በዓል፣የውጭ እንግዳ ሲቀበሉ እና በእራት ግብዣ ላይ ሁሉ ያደርጉት ንግግር በሚገባ በቀን፣በወር እና በዓመት ተለይቶ የተፃፈ መፅሐፍ ነው።መፅሐፉን በገበያ ላይ ባያገኙት በእርግጠኝነት አዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ዋና መስርያ ቤት ጀርባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቤተ መዘክር (ወመዘክር) መፅሐፍት ቤት ጎራ ብሉ አያጡትም።በእዚህ መፅሐፍ ላይ በእያንዳንዱ ዓመት  ኢጣልያ ከኢትዮጵያ ከተባረረች ጊዜ ጀምሮ እስከ 1960ዎቹ ድረስ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ወደ ውጪ አገር ለትምህርት ሲሄዱ በቅድምያ ንጉሰ ነገሥቱን ቤተ መንግስት ሄደው አግኝተው መሰናበት እና ምክር ለመቀበል ሲሄዱ ለተማሪዎቹ ያደረጉት ንግግር የመፅሐፉ አንዱ አካል ነው።በእዚህ ጊዜ ንጉሡ የሚያደርጉት ንግግር ላይ ለትምህርት የሚሄዱ ተማሪዎችን የሚሉት አንድ የተለመደ ዓረፍተ ነገር አለ። ይሄውም የወጣቶቹ ወደ ውጪ መሄድ የኢትዮጵያ ስም እንዲልቅ መሆኑን ንጉሡ ደጋግመው የሚጠቀሙበት አነጋገር ነው። ወጣቶቹ በውጭ አገር በሚቆዩበት ጊዜ ሁሉ እና በኃላ መስራት ያለባቸው ሁሉ የኢትዮጵያ ስም እንዲልቅ መሆኑን አበክረው የተናገሩበት ንግግር በተደጋጋሚ ይገኛል።የንጉሡ ምክርም ይሄው የኢትዮጵያ ስም እንዲልቅ በሚል ዓረፍተ ነገር የተሞላ ነው።ዛሬ በኦስሎ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ያደርጉት ስብሰባም የሚያስታውሰው የኢትዮጵያ ስም እንዲልቅ በሚል ሃሳብ ዙርያ ነው።

የኢትዮጵያ ስም እንዲልቅ - በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዛሬው የኦስሎ ስብሰባ  

ዛሬ ጥቅምት 8/2012 ዓም  የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ በጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ የተገኙ ኢትዮጵያውያን ታሕሳስ 10/2019 ዓም እኤአ ኦስሎ፣ኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ በተገኙበት የሚሰጠው የኖቤል ሽልማት መርሐግብር ላይ የኢትዮጵያውያን ሚና ምን መሆን አለበት በሚል ሃሳብ ዙርያ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በኖርዌይ (ኢትዮጵያ ኮሚኒቲ) ሰብሳቢ አቶ ፍቅሩ፣ከኤርትራ ማኅበረሰብ እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን የተገኙ ሲሆን በመርሐግብሩ መጀመርያ ላይ አቶ ጌታቸው በቀለ የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ ሰብሳቢ የኖቤል ሽልማቱ ከኢትዮጵያን አልፎ አፍሪካውያን የፈጠረው ልዩ ስሜት ከደቡብ አፍሪካ እስከ ምዕራብ አፍሪካ ያሉ የመገናኛ ብዙኃን በርካታ ዘገባዎች እያቀረቡ መሆኑን፣ ኢትዮጵያ የሚለው ስም ከኖቤል ሽልማቱ  በፊት በጉግል ፍለጋ የነበረው ቁጥር በአማካይ ወደ ሰላሳ አራት ሚልዮን የነበረ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ  ባለፈው ሳምንት የኖቤል ሽልማት አሸናፊ መሆናቸው ከተገለጠ በኃላ ቁጥሩ በአስር እጥፍ አድጎ ወደ ሶስት መቶ አርባ ሚልዮን  ማሻቀቡ ኢትዮጵያን በምን ያህል ደረጃ በመላው ዓለም በበጎ ጎኑ እንዳስጠራት ለማወቅ እንደሚቻል ገልጧል። 

በመቀጠል የኖቤል ሽልማት ምንነት እና በኖርዌይ የምንኖር ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁብን ስራዎች በተመለከተ ማብራርያ የሰጡት  አቶ ለማ  ናቸው። አቶ ለማ በንግግራቸው መግቢያ ላይ ሽልማቱ የፈጠረው ደስታ ታላቅ መሆኑን አውስተው፣ይህንን ታላቅ ዕድል በሚገባ በመጠቀም የኢትዮጵያን ስም ከፍ ማድረግ እንደሚቻል አብራርተዋል።በተጨማሪም የሽልማቱ ምክንያት ከኤርትራ ጋር በተፈጠረው ሰላም ብቻ ሳይሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ  በአገር ውስጥ በሰሩት መልካም ተግባር መሆኑን ካብራሩ በኃላ የኖቤል ሽልማት የሚሰጠው ድርጅት ኖቤል ኢንስቲትዩት እንደሚባል እና  የተሸላሚዎችን ታሪክ በመላው ዓለም የማስተዋወቅ ሥራ በመስራት የሕዝብ ግንኙነት ሥራ የሚሰራው  ''ኖቤል ሴንተር'' የሚሰኝ  መሆኑን አብራርተዋል።

ከስብሰባው ተሳታፊዎች በከፊል 

ከእዚህ በተጨማሪ አቶ ለማ በሶስቱ ቀናት የሚኖሩትን መርሃግብሮች በተመለከተ የሚኖሩ ክንውኖችን ከመርሐግብሩ አንፃር ሲያብራሩ፣ ታህሳስ  9/2019 ዓም ጋዜጣዊ መግለጫ ኦስሎ ላይ እንደሚሰጥ፣ በቀጣዩ ቀን ታህሳስ 10/2019 ዓም  ሽልማቱ የሚሰጥበት ቀን ሲሆን በእዚሁ እለት ምሽት ላይ በሁሉም የኖቤል ሽልማቶች ላይ እንደሚደረገው በርካታ የኖርዌይ ድርጅቶች በሕብረት  የሚያዘጋጁት በብዙ ሺህ የሚቆጠር የኖርወያውያን፣የውጭ ዜጎች እና ኢትዮጵያውያን የሚሳተፉበት የጧፍ ማብራት ሰላማዊ ሰልፍ ከማዕከላዊ ኦስሎ በተለምዶ ''ነብሩ'' ተብሎ ከሚጠራው ቦታ እስከ ግራንድ ሆቴል ድረስ እንደሚኖር እና ግራንድ ሆቴል ሰገነት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ከኖርዌይ ንጉሳውያን ቤተሰብ ጋር ብቅ ብለው  ለተሰላፊዎች የክብር ሰላምታ እንደሚሰጡ ገልጠዋል። በቀጣዩ ቀን ከእዚህ በፊት የተሸለሙ መሪዎች እንደሚያደርጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ  ከኖርዌይ ባለስልጣናት ጋር ኦፊሻል ውይይት የሚያደርጉበት ቀን ሊሆን እንደሚችል ይህ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሚኖራቸው መርሐግብር ጋር አብሮ የሚሄድ መሆኑን ገልጠዋል። ከእዚህ በተጨማሪ የኖቤል ሽልማት እንደተደረገ ዓመቱን ሙሉ ልዩ ኤግዚቢሽን ለሕዝብ ክፍት እንደሚሆን ገልጠው በመጨረሻም አቶ ለማ የአቀባበሉ ስነ ስርዓት ሁሉን በእኩልነት ያሳተፈ እንዲሆን፣ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ያለበት፣ሰንደቅ ዓላማ በተመለከተ ኦፊሻል መንገድ መጠቀም እና የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በማዕከልነት ማስተባበሩ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። 

በመቀጠል የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሰብሳቢ አቶ ፍቅሩ ይህንን ስብሰባ ያዘጋጀው የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክን  አመስግነው፣የኖቤል ሽልማቱ የተሰጠበት ቀን ኮሚኒቲው ምሽቱን ጥሪ አድርጎ ደስታውን በአንድነት መግለጡን  እና በዕለቱ ከኖርዌይ ቴሌቭዥን ዘጋቢዎች መገኘታቸውን ገልጠዋል።ከእዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ኮምኒቲ  የኖቤል ሽልማት ዝግጅት በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ለማግኘት ጥረት ማድረጉን እና ኤምባሲውም በራሱ መረጃ እየጠበቀ መሆኑን እንደገለጠ አስታውቀዋል።ከእዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የምንም እና ማንም የፖለቲካ ድርጅት አቀንቃኝ አለመሆኑን አፅንኦ ሰጥተው አሁንም ከሁሉም ስብስቦች ጋር  ለመገናኘት እየሞከረ መሆኑን ገልጠዋል።

ስብሰባው በተከታይ በኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ ሰብሳቢ አቶ ጌታቸው በቀለ አወያይነት ተሰብሳቢዎቹ በኖቤል ሽልማቱ ስነ ስርዓት ሰሞን በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሚና እና የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በማገዝ ሊሰሩ የሚገባቸው ስራዎች ዙርያ  ተሰብሳቢዎቹ ሃሳብ ሰጥተዋል። ከተሳታፊዎች ከተሰጡት ሃሳቦች ውስጥ -

'' እኔ በሕይወቴ ያላየሁት ጉዳይ ነው ያየሁት'' አሉ አንድ እናት ስለ ኖቤል ሽልማቱ ሲናገሩ በመቀጠል '' ዜናው ሲነገር ነጮቹ ድንገት መጥተው  ከበቡኝ እየሳሙ 'ግራቱለረ' የምስራች! አሉኝ።ቀኑን ሙሉ ስሳም የዋልኩት፣ልጄ ድንገት ደውሎ 'ግራቱለሬ' ማሚ ብሎ ደስታው ሲቃ እየተናነቀው አናገረኝ።ትምህርት ቤቱ ተማሪው ሁሉ ከቦት ደስታውን እየገለጡለት እንደሆነ  ነገረኝ።ይህ ብቻ አይደለም።የትምህርት ቤቱ የክፍል ልጆች ጋር ተሰብስበው በዓል አደረጉ።ይህ ጉዳይ በልጆቻችን ላይ የፈጠረው የሞራል ልዕልና  በቃላት የምገልጠው አይደለም።እባካችሁ ልጆቻችን የኢትዮጵያን መከራ ስናወራ ሲሰሙ ነው ያደጉት። ቢያንስ ደስታ እስኪ የሚሰሙበት ጊዜ እንዲሆን ይህንን የኖቤል ሽልማት አስመልክቶ አንድ አይነት  ትልቅ ዝግጅት ማዘጋጀት አለብን።ይህንን ዝግጅት ላይ ለመገኘት የኖርዌይ ተወላጆች ሁሉ እየጠየቁ ነው እና ይህ ጉዳይ  ሊታሰብበት ይገባል'' ብለዋል።

ሌላ እናት ቀጠሉ '' የሽልማቱ ቀን በርካታ ቴክስት ከኖርዌይ ተወላጆች ደረሰኝ።ብዙዎቹ የጉዲፈቻ ኢትዮጵያውያንን ያሳደጉ ናቸው። ሁሉም የሚያሳድጉዋቸው ልጆች ይህንን ደስታ የሚያሳዩበት አንድ አይነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚገናኙበት  የጋራ ደስታ መግለጫ በዓል እንዲዘጋጅ እና በእዚህ ዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ቃል ገብተዋል። ስለሆነም እባካችሁ ከእኛ ይልቅ ልጆቻችን የሚኮሩበት እና በአገራቸው የሚኮሩበት መልካም ዕድል እንፍጠር'' ብለዋል።


ስብሰባው በመቀጠል ከኤርትራ ማኅበረሰብ የመጡ አቶ ንጉሡ አስተያየት የሰጡ ሲሆን በአስተያየታቸው ''እኔ አሁን ኤርትራ ቀድሞ የኢትዮጵያ ክፍለ አገር የመጣሁ የዓቢይ ወጤት ደጋፊ ነኝ።አብረናችሁ ነን።ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አንድ ሕዝብ ነን በእዚህ  ዝግጅት ላይም አብረናችሁ ነን'' ብለዋል።

በመጨረሻም  ስብሰባው ከመጠናቃቁ በፊትበሚከተሉት ነጥቦች ላይ የጋራ መግባባት ተደርሶበት  ስብሰባው ተፈፅሟል። እነኝህ በጋራ መግባባት የተደረሰባቸው ነጥቦች -

  • የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ቀድም ብሎም እንደገለጠው ከኖቤል ሽልማቱ ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ወደ ኦስሎ ሲመጡ ለሚኖረው የክብር አቀባበል፣እስከ የሚመለሱበት ጊዜ ያለው ዝግጅት ዙርያ የሚያስተባብር አንድ ግብረ ኃይል  በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ እንዲመሰረት እና ወደ ሥራ እንዲገባ፣ይህ ኮሚቴ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን፣
  • የኢትዮጵያ ኤምባሲ (ስዊድን ፣ስቶኮልም የሚገኘው) ከኢትዮጵያ ኮሚንቲ ጋር አብሮ እንዲሰራ እና ዝግጅቱ ውበት ያለው እንዲሆን መስራት እንዲጀመር፣
  • ኢትዮጵያን ባላቸው የግልም ሆነ የቡድን ግንኙነት (ኔትዎርክ) የኖቤል ሽልማቱ ለኢትዮጵያ ትልቅ ስም የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን  ይህንን ታሪካዊ እና አገራዊ ፋይዳ ያለው ዝግጅት በኢትዮጵያዊ ጨዋነት  እና በባለቤትነት እንዲያስተናግዱ እና  አስፈላጊውን ጥሪ ከኮምንቲ እንዲጠብቁ፣
  • አንድ ልዩ የደስታ መግለጫ መርሃግብር ሁሉንም ኢትዮጵያውያን፣አፍሪቃውያን እና የኖርዌይ ተወላጆች የሚያሳትፍ ዝግጅት እንዲኖር  በእዚህ ዝግጅት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የሚገኙበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይም  ኢትዮጵያውያንን የሚያገኙበት መልካም አጋጣሚ እንዲፈጠር የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ነበሩ።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በተሰጡት ሃሳቦች ዙርያ አስተያየት ከሰጠ በኃላ በስብሰባው መደሰቱን እና በርካታ ጠቃሚ ግብዓቶች  መገኘታቸው እና አሁንም በዝግጅቱ ማማር ዙርያ ሁሉም ኢትዮጵያውያን አብረው እንዲሰሩ እና በተቀናጀ መልክ  ለመስራት እና የኢትዮጵያን ስም ከፍ ለማድረግ ለመስራት ጥሪ አቅርቦ የዕለቱ ስብሰባ ተፈፅሟል። 


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church is in turmoil in Athens, Greece.

His Holiness Abune Mathias I, Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, met with Greece's Ambassador to Ethiopia, Antonios Sg...