Wednesday, January 22, 2020

Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) Filling Scenarios: Analysis of Energy and Revenue losses

Photo - Ethiopian New dam on Nile (file)
ስንቶቻችን Ethiopian International Professional Support for Abay (EIPSA) እናውቀዋለን ? በእዚሁ ድረ ገፅ ላይ ኢትዮጵያውያን ምሁራን ዶ/ር በላቸው ተስፋ እና ዶ/ር ምንትዋብ በዛብህ (Dr. Belachew Tesfa and Dr Mintwab Bezabih) የፃፉት አዲስ አርቲክል ከእዚህ በታች ተያይዟል።
=========================================
The above titled article is taken from the Ethiopian International Professional Support for Abay (EIPSA). 
First of posting an article, Gudayachn would like to introduce you the professional support team. Here is the an introduction paragraph obtained from the Professional Support's page.
The Ethiopian International Professional Support for Abay (EIPSA) established on the 22, June 2013, in response to the timely need for an organized and independent professional Ethiopian voice surrounding the issue of the Nile River. The majority of the Nile River flow originates in Ethiopia and carried downstream by Blue Nile, while a much smaller portion comes from the White Nile. Both rivers meet in Khartoum to form the Nile. Despite its lion share contribution to the Nile River flow, Ethiopia has never benefited from its waters for a number of reasons. Therefore, the start of the construction of the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) virtually remains Ethiopia’s only effort in its attempt to make use of the Blue Nile waters.
================================
Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) Filling Scenarios: Analysis of Energy and Revenue losses 
By Dr Mintwab Bezabih1 and Dr Belachew Tesfa
International Journal of Nile Basin (IJNB) Energy, Water, Environment & Economic Volume 3; Issue 5; December 2019, Page 1-11
To read the whole article, please click on the below link -
http://www.eipsa1.com/cms/articles/GrandEthiopianRenaissanceDam(GERD)FillingScenariosAnalysisOfEnergyBezabihandTesfa_Dec2019.pdf

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Monday, January 20, 2020

የጥምቀት ብሔራዊ በዓላችንን ደስታ ለመንጠቅ የፈለጉ አልተሳካላቸውም። የስነ-ልቦና ዘመቻቸው ሙሉ በሙሉ ከሽፏል!



  • ሳትሰለፍ እና ሳትለፈልፍ ኢትዮጵያዊ የሞራል ልዕልናህን የምትሰቅልባቸው ቀላል መንገዶች በእዚህ ፅሁፍ ውስጥ ተካተዋል።ሕዝብ አንቂዎች ሃሳቡን ወስደው በግዙፍ መልክ ሊያንቀሳቅሱት ይገባል።


ጉዳያችን / Gudayachn
ጥር 11/2012 ዓም (ጃንዋሪ 20/2020 ዓም)

=============
የጥምቀት በዓል ባብዛኛው ተጠናቋል:: የቅደሰ ሚካኤል ታቦታት ግን ነገ ቃና ዘገሊላ በዓል ስለሆነ እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ወደ መንበራቸው ይገባሉ::እነኝህ ታቦታት ደግሞ ሌላው ጋር ለማጀብ ሄዶ የነበረው ምዕመን በብዙ እጥፍ ሆኖ የሚያጅባቸው ታቦታት ናቸው።በዘንድሮው ጥምቀት ባብዛኛው በሚያስደስት መልኩ ተፈፅሟል::እንደ ሆሳዕና ያሉ ቦታዎች ችግር ለመፍጠር ሙከራ ተደርጎ ከሽፏል::ከእዚህ ተምረናል::
ሐረር ስርዓት አልበኞች ታቦታቱን ለማስቆም ሞክረዋል÷የክልሉ ፖሊስ ድርጊት ህዝብ አሳዝኗል÷ሰው ቆስሏል በእዚህ አዝነናል::ሁሉም በእምነቱ ለማይገፋባት ኢትዮጵያ የበለጠ መስራት እንደሚገባ ከምን ጊዜውም በላይ ግልጥ ሆኗል::

መንግስት በተቻለ ለጸጥታው መጠበቅ መድከሙ ይታወቃል::በክልል ደረጃ ያሉት የጸጥታም ሆነ የአመራሮች ዘገምተኛ እና የግል ፍላጎታቸውን በአመራር ስልጣናቸው ላይ ለመጫን ሲሞክሩ እና ችግር ሲፈጥሩ ታይተዋል።በአጠቃላይ መንግስት ያደረገው ዝግጅት ብቻ ሳይሆን የህዝቡ በተለይ የወጣቱ የትቀናጀ የመረጃ አሰራር ሁሉ በራሱ ይህ የጥምቀት በዓል አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።እያንዳንዱ የሚጠበቅበት ገብቶታል።ኃላፊነት ተሰምቶታል።ለአገሩ ሰላምም ሆነ ለሁሉም ዕምነት በእኩል አገሬ ብለው የሚኖሩባት ኢትዮጵያን ለማጠልሸት የሚፈልጉ ስርዓት አልበኞች ችግር ለመፍጠር መሞከራቸው በራሱ አስተማሪ ነው።

ጉዳዩ ስነ ልቦናዊ ጦርነት ነው 

በጥምቀት ሰሞን ከሆነው አንዱ የፕሮፌሰር መራራ ኦፌኮ ጀዋርን እና በኦሮምያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ለመከፋፈል የቤት ሥራ የተሰጠው ዲያቆን ኃይለ ሚካኤል የተባለ ግለሰብ በሰላሌ የምርጫ ቅስቀሳ በሚል ከከተራ አንድ ቀን ሲቀረው ጀዋርን ከጀርባው አቁሞ (ጀዋር በደስታ ሲፍነከነክ ይታያል)  የኦሮሞን ሕዝብ በራሱ የሚከፋፍል፣በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ግልጥ የሆነ ጦርነት አውጁአል።

በእዚሁ ንግግሩ ላይ የደብረ ሊባኖስን ገዳም ሳይቀር ቃል በቃል ጠቅሶ ''ሕዝብ ሰብሮ እንዲገባ'' መልዕክት አስተላልፏል።ከእዚህም በተጨማሪ ''ቤተክርስቲያን የፊውዳሎች  የፖለቲካ ኤምባሲ ነች'' በማለት  ሲናገር ተሰምቷል።እነኝህ የጥላ ንግግሮች የሚናቁ የጥላቻ ንግግሮች አይደሉም።ሆኖም ግን ዋና ግባቸው ስነ ልቦናዊ ጦርነት በኢትዮጵያውያን ላይ መክፈት ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም ብሎም ለማጥፋት እንዲሁም ከሕዝቡ ጋር ለማጋጨት በብዙ ትውልዶች ተሞክሯል።ግን አልተቻለም።ባለመቻሉም ቅድምያ የስነ ልቦና ጦርነቱ ተመራጭ ሆኖ ለጥፋት ኃይሎች ታይቷቸዋል።በቅድምያ ግን የእዚህ አይነት የምርጫ ቅስቀሳ  እየሰሙ ዝም ያሉት የምርጫ ቦርድ፣  የማዕከላዊው መንግስት፣የኦሮምያ ክልል ባለሥልጣኖች፣ በኦፌኮ፣በጀዋር፣በዲያቆን ኃይለ ሚካኤልም ሆነ የጥላቻ ዘመቻ ባስተላለፉት የኦኤምኤን ሚድያ ላይ ምንም ዓይነት ሕጋዊ ርምጃ ባለመውሰዳቸው በሕግ ያስጠይቃቸዋል።ይህ ጉዳይ ደግሞ በተከታይ በሚፈጠሩ ችግሮች ምርመራ ላይ መነሻው ወደኃላ ሲሄድ እንደ ኦፌኮ የምርጫ ዘመቻ ንግግሮች መሆናቸው ድምዳሜ ላይ ስለሚደረስ መቼም መቼም ከፍርድ ማምለጥ አይቻልም።ለእዚህ መፍትሄው በፍጥነት የማያዳግም ሕጋዊ ርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል።ርምጃው በመግለጫ ጋጋት የሚፈታ አይደለም።ተግባራዊ ሕጋዊ ርምጃ የመንግስት አካላት ማሳየት ግዴታቸው ነው።ይህ ካልሆነ አብረው ይጠየቃሉ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን የስነ-ልቦና ዘመቻውን ግብ እና መነሻ በሚገባ ተረድቶ ዘመቻውን ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ ነው ያለበት።የፅንፍ ኃይሎች ዋነኛ መለያቸው የበታችነት ስሜት መሰቃየታቸው ነው። ይህንን የበታችነት ስሜት ስቃይ የሚያስታግሱት ድሮ እንዲህ የሚባል ሰው እዚህ ቦታ አንድ ዛፍ ተክሎ ነበር አሉ እና የመሳሰሉ ታሪኮች እያነሱ አሁን ያለውን ሕዝብ የምያጋጩበት ታሪኮች በመተረክ ነው።በእዚህ አሁን ያለውን ሕዝብ ስነ-ልቦና ያሸበሩ እንደሆነ ያስባሉ።ያልተገነዘቡት ነገር ግን ይህ አካሄድ ሁለት ነገር ይዞ እንደሚመጣ ነው።አንድ፣ከምር የዛፉ ተካይ ታሪክ ሕዝብ ዛሬ አይጠቅም ብሎ ያሰበውን ታሪክ ይዞ የወጣ ቀን የፈሩት የበታችነት ስሜት በከፋ መልኩ እንደሚከሰት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ህዝቡ በበለጠ እርስ በርሱ እንዲከባበር እና የመርዘኞች አካሄድ አደጋ ከማምጣቱ በፊት እነርሱን ለማሳፈር እንደሚነሳ ነው።

ኢትዮጵያውያን ወደፊትም ሞራላዊ እና ስነልቦናዊ ልዕልናችሁን ስቀሉባቸው!

የዘንድሮ 2012 ዓም  የጥምቀት በዓል በብዙ የኢትዮጵያ ክፍሎች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከምንጊዜውም በላይ ደምቆ ወጥቶ በነፃነት ተከብሯል።ከጅጅጋ እስከ አርባንምጭ፣ከጋምቤላ እስከ መቀሌ፣ከሞያሌ እስከ ጉጂ ዞን፣ከሐዋሳ እስከ አሶሳ፣ከጎንደር እስከ ከሚሴ፣ከአዲስ አበባ እስከ ባሌ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከታቦታቱ ጋር በድምቀት ታይቶ ተከብሯል።ይህ በእንዲህ እያለ የስነ ልቦና ጦርነቱን ለማድረግ ከፅንፈኛ ኃይሎች ድርጎ የለመዱ በአንዳንድ ቦታዎች በተለይ በአብዛኛው የኦሮምያ ክልል የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ሲያስወርዱ፣ሪባን ጭምር እንዳትይዙ በሚል ችግር ፈጥረዋል።ድርጊቱ የጥቂቶች ብቻ ሳይሆን በመንግስት የፀጥታ መዋቅር ውስጥ ያሉ ሁሉ የድርጊቱ ተሳታፊ ሆነዋል።ይህ በህጋዊ መልኩ ሲታይ የመንግስት ግልጥ ክስረት ያሳያል።በመጀመርያ ደረጃ ጉዳዩን በተራ የአስተሳሰብ ልክ ብናስበው  ግለሰብ በራሱ የፈለገውን  የቀለም ሕብር የመያዝ መብት አለው። ቤተክርስቲያን እንደ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የተለየ መብት አላት።ለግለሰብ መከልከል የማትችለውን መብት ለተቁአም ልትከለክል አትችልም።የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ደግሞ የክርስቲያን ወይንም የሙስሊም አልያም የአይሁድ ዕምነት መለያ አይደለም።የክርስትናም፣የእስልምናም ሆነ የአይሁድ አባት በኖህ ዘመን ከሰማይ የተሰጠ በሁሉም የሰው ዘር እና በእግዚአብሔር መካከል የተገኘ ቃል ኪዳንን መነሻ ያደረገ ነው።ይህ ማንንም ሊያጣላ አይችልም።

በተግባር የሞራል ልዕልናው እንዲህ ይሰቀላል

በመቀጠል የልዕልናውን ደረጃ መስቀል ተገቢ ነው።እንዴት? ለሚለው 
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ምንም ምልክት የሌለበት ሱቅ ምንም ዓይነት ግብይይት ባለማድረግ፣የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላም የሌለው ማንኛውም ምግብ ቤት ሳትቃወመው ከራስህ ጋር ተነጋግረህ ፈፅሞ ግብቶ አለመመገብ፣የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በትንሹም ቢሆን ሻጥ ያደረገች የጉልት ቸርቻሪም ብትሆን ደጋግሜ በመግዛት ስፈልግ የፈለኩትን ያህል ገንዘብ በመጨመር፣የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላም የማይታይበት የቴሌቭዥንም ሆነ የፖስተር ማስታወቂያ መንግስታውም  ቢሆን ፈፅሞ እንደማልቀበለው እና ባለመግዛት፣የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የማይታይበት ማናቸውም መጠጥም ሆነ የስነ ጥበብ ዝግጅት፣ልብስም ሆነ ማስቲካ ሳይቀር  አለመግዛት።ሳትሰለፍ እና ሳትለፈልፍ ኢትዮጵያዊ የሞራል ልዕልናህን የምትሰቅልባቸው ቀላል መንገዶች ከላይ የጠቀሱት እንደመነሻ ተነስተዋል።ወደፊትም በበለጠ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በገነት እና በሲኦል ሳይቀር ቅዱሳኑም ሆኑ ርኩሳኑ መናፍስት እስክገርማቸው ድረስ አብዝተህ አሰራጨው።ማንም ከፈለገ ከሲኦል ወይንም ከገነት ውጪ ዓለም ካለ ወደዚያ  የመሄድ መብቱን እናከብርለታለን።


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

ከሁለት ሚልዮን በላይ እንግዳ የታደመበት  የ2012 ዓም ጥምቀት በዓል አከባበር  በጎደር የቀጥታ ሙሉ ስርጭት ቪድዮ

ከዓማራ መገናኛ ብዙሃን የተወሰደ


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Saturday, January 18, 2020

በኢትዮጵያ የ2012 ዓም የጥምቀት በዓል አከባበር ዝግጅት ብዙ ነገሮች አመላካች ሆኗል።ዝግጅቱ በኦሮምያ ፣ሆሳዕና ፣አርባምንጭ፣አዲስ አበባ፣ ጎንደር ምን ይመስላል? (ፎቶዎች ይመልከቱ)

ጉዳያችን ዜና /Gudayachn News
ጥር 9/2012 ዓም (ጃንዋሪ 18/2020 ዓም)

በኢትዮጵያ የጥምቀት በዓል ከእሁድ ጥር 10 ጀምሮ እስከ ጥር 12 ድረስ ይከበራል።በዓሉ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የተላያዩ መልክ ይዟል።የበዓሉ አከባበር በራሱ የብዙ ነገሮች አመላካች ሆኗል።

- በኦሮምያ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከሪባን ጀምሮ ተከልክሎ ሕግ የሚያስከብር ጠፍቷል።ሻሸመኔ ዋና ማሳያ ሆናለች።በኦሮምያ ያሉ የክልሉ ተወላጆች የክልሉ የፀጥታ ኃይል ከፍተኛ በደል እየፈፀመባቸው ነው የሚናገሩት።በውጭ አገር ኢትዮጵያውያን የቤተ ክርስቲያኒቱን ዓርማ መስቀል ያልተከለከሉትን በአገራችን ተከለከልን የሚል ምሬት ይሰማል።ጉዳዩ በኦሮምያ የሕግ መጥፋት አመላካች ሆኗል።አብዲሳ አጋ፣ጃጋማ ኬሎ እና ብዙ ሚልዮኖች የሞቱላት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ዛሬ በኦሮምያ ጥምቀት በዓል ላይ እንዳይታይ መደረጉ የክልሉ አስተዳደር ከፅንፍ ኃይሎች ጋር እየሰራ ለመሆኑን ማሳያ ነው የሚሉ በርካታ የኦሮምያ ክልል ነዋሪዎች አሉ።

- ሰሜን ሸዋ ፍቼ ዛሬ ረፋዱ ላይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ መስቀል የተከለከሉ ወጣቶች ተፋጠዋል።በጣልያን ሰማዕትነት የተቀበሉት የአቡነ ጴጥሮስ አገር ፍቼ ሰንደቅ ዓላማ መስቀል ተከልክላ ከተማው ውጥረት ላይ ነች የሚለው ዜና በራሱ የክልሉ አደገኛ አካሄድ አመላካች ነው።

- በሆሳዕና ህዝቡ ለረጅም ጊዜ የጥምቀት በዓል ማክበርያ ቦታ ጠይቆ የከተማው አስተዳደር ከልክሎት እስከ ደቡብ ክልል ድረስ አቤት ብሎ  ክልሉ 20ሺህ ካሬ ፈቅዶ ለሆሳዕና ከተማ ምክርቤት ደብዳቤ ከፃፈ ሳምንት ቢሆነውም እስከ ትናንት ምሽት ድረስ ኮሚቴው  ቢጠብቅም የከተማው ምክርቤት ጉዳዩን በመከልከሉ የአገረ ስብከቱ ዘንድሮ በሆሳእና ጥምቀት አለመኖሩን በሃዘን ገልጦ ደብዳቤ አውጥቷል።ጉዳዩ ከፍተኛ ውጥረት ፈጥሯል።በመላው ኢትዮጵያ የሚኖሩ  በየትኛውም ቦታ ጥምቀት የሚያከብሩ ሆሳዕናን እንዲያስቡ በማኅበራዊ ሚድያ ጥሪ እየተላለፈ ነው።

-  በጎንደር ከሰላሳ ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ጨምሮ እስከ ሁለት ሚልዮን ሕዝብ ለበዓሉ እንደምታደም ተገልጧል።በተለይ የጎብኚው ቁጥር እስከ ሁለት ሚልዮን እንደሚደርስ የዘገበው የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የከተማዋን  ባለስልጣናት ጠቅሶ ነው።

- በአርባምንጭ፣አዲስ አበባ እና ጋምቤላን ጨምሮ በዓሉ በደመቀ ሁኔታ ሊከበር ከፍተኛ ዝግጅት ላይ ነው።
ከእዚህ በታች ያሉት ፎቶዎች ለታሪክ የሚቀመጡ ናቸው።


ሻሸመኔ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ያለው ሪባን ተከልክሎ ህዝቡ ይህንን እንዲሰቅል ተገዷል።
የሆሳዕና ምእመናን የጥምቀት በዓል ማክበርያ ቦታ ተከልክለው በሃዘን ተቀምጠው።

 አዲስ አበባ ጎዳናዎች እንዲህ ደምቀዋል ቻይናውያን ሳይቀሩ 
 አርባምንጭ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ 
 አዲስ አበባ ተክለሃይማኖት አካባቢ 
 ጋምቤላ ዛሬ 
 ጋሞዎች ጥምቀት ለማክበር ጎንደር ቀርበዋል። 
 ጋሞዎች ለጥምቀት በዓል  ወደ ጎንደር ሲገቡ 
 የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የሚልዮኖች ሰማዕታት ውጤት ጎንደር ላይ እንዲህ በእናቶች ተስማለች።
 ጎንደር ለጥምቀት በዓል ዝግጅት ሙስሊም ወገኖቻችን ከክርስቲያኖች ጎን አብረው ሥራ ላይ 

 አዲስ አበባ ተክለሃይማኖት አደባብይ ላይ የተሰራው የታቦት ማደርያ በወጣቶች የተሰራ 
  አዲስ አበባ ተክለሃይማኖት አደባብይ ላይ የተሰራው የታቦት ማደርያ በወጣቶች የተሰራው በምሽት ይህን ይመስላል።
 አዲስ አበባ ተክለሃይማኖት አደባብይ ላይ የተሰራው የታቦት ማደርያ በወጣቶች በሥራ ላይ እያለ 


ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Thursday, January 16, 2020

የሰሞኑ የዋሽንግተኑ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድር በጥሩ ሁኔታ መፈፀሙን የሶስቱም አገሮች ልዑካን አስታወቁ።Ethiopia,Egypt and Sudan officials say they have reached a preliminary agreement on Ethiopian Renaissance Dam negotiation in Washington D.C

ሰባ በመቶ የተጠናቀቀው የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ  

ጉዳያችን ዜና /Gudayachn News
ጥር 7/2012 ዓም (ጃንዋሪ 16/2020 ዓም)

በዋሽንግተን ካለፈው ሰኞ ጀምሮ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙርያ በኢትዮጵያ፣ግብፅ እና ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የውሃ ሚኒስትሮች መካከል ሲደረግ የነበረው ድርድር በጥሩ ሁኔታ ማለቁን የሶስቱም አገሮች ልዑካን በሰጡት የጋራ መግለጫ አስታውቀዋል።በድርድሩ ላይ የአሜሪካ የገንዘብ ሚኒስትር ስቴቨን ምንቺን እና የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስ ተገኝተዋል።

የግድቡ ሥራ 70% መጠናቀቁ የተነገረው የታላቁ የአባይ ግድብ አወዛግቦ የነበረው ግብፆች ባነሱት የውሃው የመሙላት ጊዜ ላይ እና የድርቅ ወቅት በሚለው ትርጉም ላይ ነበር።በእዚህ መሰረት በአሁኑ ስምምነት ኢትዮጵያ በጠየቀችው መሰረት የግድቡ መሙያ ጊዜ ድረጃ በደረጃ የሚፈፀም ሆኖ በዋናው የኢትዮጵያ የዝናብ ወቅት ማለትም ከሐምሌ እስከ ነሐሴ ሆኖ እንደአስፈላጊነቱ መስከረምን ሊሻገር እንደሚችል ተስማምተዋል። የድርቅ ወቅት የሚለውን ትርጉም እና በእነኝህ ወቅት የሚወሰዱት ርምጃዎች በተመለከተ ሶስቱም አገሮች በሰጡት መግለጫ የድርቅ ወቅት  በተመለከተ በሶስቱም አገሮች በጋራ የሚወሰድ የጋራ ኃላፊነት እንደሚሆን እና የድርቅ ጊዜውን እንዴት እንደሚይዙት  እና እንደሚወጡት በጋራ ገምግመው እርምጃ የሚወሰድ እንደሆነ ነው የተነገረው።ይህንን አስመልክቶ የሶስቱ አገራት ልዑካን በሰጡት መግለጫ ላይ -

''ተደጋጋሚ ድርቅን እና ጊዚያዊ ድርቅን በተመለከተ አያይዙን ሶስቱም አገሮች በጋራ ኃላፊነት ይወስዳሉ'' 
''There is a shared responsibility of the three countries in managing drought and prolonged drought,''

የጋራ መግለጫው እንደገለጠው ይህ የአሁኑ መግባባት ግድቡን በተመለከተ የመጨረሻ ስምምነት ሳይሆን በቀሪ ነጥቦች ላይ ውይይቱ ዋሽንግተን ላይ ጃንዋሪ 28-29/2020 ዓም እኤአ እንደሚቀጥል ተነግሯል።

በሌላ በኩል የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በትውተር ገፃቸው በእንግሊዝኛ ባሰፈሩት ፅሁፍ 

''የታላቁ የህዳሴ ግድብ በተመለከተ አስፈላጊ እና ወሳኝ ውጤት አግኝተናል።ከጎናችን የቆማችሁ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በሙሉ እናመሰግናለን።በድርድሩ ያገኘነውን ውጤት ወደ ሕጋዊ ሰነድ እና መመርያዎች ይቀየራሉ'' ብለዋል።


ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church is in turmoil in Athens, Greece.

His Holiness Abune Mathias I, Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, met with Greece's Ambassador to Ethiopia, Antonios Sg...