ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, August 21, 2018

ያለፈው የአርባ ዓመታት የመለያየት ፖለቲካን ለአዲሱ ትውልድ የማገናኘት ሥራ ሰጥቷል።ልብ የሚነካ ታሪክ (ቪድዮ)

ያለፈው ትውልድ የአቶ ኢሳያስ እና አቶ መለስ ትውልድ የዘራው የመለያየት ፖለቲካ ለአሁኑ ትውልድ አካላት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ፣ጋዜጠኛ 'ጆሲ' እና ለሌሎችም የማገናኘት ሥራ ላይ እንዲጠመዱ አስገድዷል።ይህ ለአሁኑ ትውልድ አካላት የተሰጠ ዕድል ነው ማለት ነው።ያለፈው ሥራ ለአሁኑ ዕዳ የሚሆንበት ጊዜ አለ።የአሁኑ ትውልድ አካል ሆነን ያለፈው ትውልድን የማለያየት ፖለቲካ እንዳናራምድ እንጠንቀቅ።ያለፈው ይብቃ።ይህንን ቪድዮ ተመልከቱ እና የተሳሳተ ፖለቲካ ተራው ሕዝብ ላይ የሚፈጥረውን ቀውስ እንመልከት።
ልብ የሚነካ ታሪክ - አባት የቀድሞ ጦር ሰራዊት አባል፣ እናት የአስመራ ልጅ፣ ልጆች አዲስ አበባ እና አስመራ ተለያይተው አደጉ።እንዴት ተገናኙ? ሲገናኙ የነበረው ስሜትስ? (ቪድዮው ላይ ይመልከቱ)

ምንጭ : - ጄቲቪ  (ጄ ቴሌቭዥን)



ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...