Wednesday, April 18, 2018

ከእመቤቴ ሌላ የምጠራው ምስክር የለኝም ሁሉን የማማክራት ገመናዬን ሸፋኝ እርሷ ነች፣ አርቲስት መሰረት መብራቴ ከሰርግ ስነ ስርዓቷ በኃላ እያለቀሰች የተናገረችው (ሙሉ ቃለ ምልልሱን ያዳምጡ)

ጉዳያችን / Gudayachn
ሚያዝያ 10/2010 ዓም (አፕሪል 18/2018)

''ክርስቲያን በሁለት ሰይፍ የተሳለ ነው።በመንፈሳዊ ሕይወትም ፊት አውራሪ በስራውም ጎበዝ መሆን አለበት'' አርቲስት መሰረት መብራቴ

አርቲስት መሰረት መብራቴ በኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ቀዳሚ ከሚባሉ አንስት ተዋናይ ውስጥ ነች።መሰረት በኪነጥበቡ ዓለም ጠንካራ ስብዕና፣ የጎላ ኢትዮጵያዊ ለዛ እና መልካም ስነ ምግባር የሕይወቷ ፍልስፍናዎች እንደሆኑ በተለያዩ ጊዜ በሰጠቻቸው ቃለ መጠይቆች ገልጣለች።ባለፈው ሳምንት  አዲስ አበባ የድምፃዊት  እጅጋየሁ ሽባባው ወንድም ከሆነው ከአቶ ዘውዱ ሽባባው ጋር የጋብቻ ስነስርዓቷን ፈፅማለች።ሰይፉ ፋንታሁን በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ቃለ መጠይቅ አድርጎላት ነበር።
የቃለ መጠይቁን ሙሉ ቃል እና የአርቲስት መሰረትን መንፈውሳዊ መዝሙር በተከታታይ ከእዚህ በታች ያዳምጡ።


የአርቲስት መሰረት መብራቴ መንፈሳዊ መዝሙር 

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...