ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, June 12, 2017

አርበኞች ግንቦት 7 ለመጀመርያ ጊዜ አዲስ አበባ ላይ ጥቃት መፈፀሙን ገለጠ

Patriotic-Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy attacks TPLF´s secret torching house and armament store in Addis Ababa 

የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ለመጀመርያ ጊዜ አዲስ አበባ ከተማ  ውስጥ በሚገኝ የስርዓቱ የሚስጥር ማዕከል ላይ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ።ጥቃቱ የተፈፀመው የቀድሞው ናዝሬት አውቶብስ ተራ አጠጋብ በሚገኝ የሕወሓት ድብቅ ማሰቃያ እና የመሳርያ ማከማቻ ላይ መሆኑን ይገልጣል።ይህ በአዲስ አበባ የድርጅቱ ሴል በኩል መፈፀሙ የተገለጠው ጥቃት የሚስጥር ማሰቃያ ቤቱንም ሆነ የመሳርያ ግምጃ ቤቱን ሙሉ በሙሉ እንዳወደመው እና ውድመቱ በቶሎ ሳይጠፋ መቆየቱን እና የአዲስ አበባ ህዝብም ለሰዓታት እንዲመለከተው መደርጉን ዜናው ያብራራል።

ድርጅቱ ለኢሳት ራድዮ እና ቴሌቭዥን ዛሬ ሰኔ 5፣2009 ዓም በላከው ዜና ላይ መለቀቁን ለማወቅ ተችሏል።ከእዚህ በተጨማሪ ድርጅቱ በሰሜን ጎንደር የተለያዩ ቦታዎች በስርዓቱ ወታደራዊ ኃይል ላይ ጥቃት መፈፀሙን እና ከስልሳ በላይ እስረኞችን ማስለቀቁን ገልጦ ነበር።ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሕወሓት በኩል የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች በፈቃዳቸው ወደ መንግስት እጃቸውን ሰጡ የሚል ዜናም የተለቀቀው ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ ነበር።

በሌላ በኩል የመንግስት የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ የሚለው ዜና ድርጅቱ ጥቃት የመፈፀሙ አፀፋ ፕሮፓጋንዳ ሆኖ መቅረቡ በትክክልም አንድ አይነት ግጭት መኖሩን አመላካች ነው የሚሉ ብዙዎች ናቸው።የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ላለፉት ሁለት የሳምንታት መጨረሻዎች በሰሜን አሜሪካ እና ካናዳ በተዘጋጁ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ንግግር ማድረጋቸው ሲታወቅ በያዝነው ሳምንት ቅዳሜ ሰኔ 10 ኦስሎ ኖርዌይ፣ ሰኔ 11 ደግሞ በስዊዘርላን ተመሳሳይ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ላይ እንደሚገኙ ከድርጅቱ የወጡ ዘገባዎች ጠቁመዋል።

ከእዚህ በታች አባይ ሚድያ ላይ የአዲስ አበባውን ጥቃት አስመልክቶ የወጣው ዜና ነው። 





ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።