Friday, June 16, 2017

ሰበር ዜና - አዲስ አበባ የሚለውን ስም እና የጎዳናዎቿን ስም ለመቀየር በሕወሓት የሚታዘዘው የኢህአዴግ ምክር ቤት ዛሬ ስብሰባ ይቀመጣል



ሃያ አባላት እንደቀሩት የሚነገረው በሕወሓት የሚታዘዘው የኢህአዴግ ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 10፣2009 ዓም የአዲስ አበባን ስም ወደ ፊንፊኔ ለመቀየር፣የአዲስ አበባ ጎዳና ስሞችን በኦሮሞ ታሪክ ስሞች ለመቀየር፣የአዲስ አበባን የስራ ቋንቋ ኦሮምኛ ለማድረግ፣የኦሮምኛ ተናጋሪዎች አዲስ አበባ ላይ መሬት ካለ ሊዝ እንዲወስዱ ለመፍቀድ እና በአዲስ አበባ ውስጥ ያሉ ሁሉም መስሪያ ቤቶች ሥራ አስኪያጆች በኦሮሞ ተወላጆች ለመቀየር በሚሉ የውሳኔ ሃሳብ አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር ለማወቅ ተችሏል። ዜናውን ከአስተማማኝ ምንጭ መገኘቱን የኢሳት ራድዮ እና ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ በእየፊናቸው ሰኔ 9፣2009 ዓም ምሽት ገልጠዋል።

ሕወሓት አዲስ የመነታረኪያ አጀንዳ ለመሃል ሀገር ለመስጠት እና በዐማራ ክልል የተነሳበትን ብረት ያነሳ ሕዝባዊ ኃይል ለመዋጋት ያቀደ ይመስላል።አሁን በአዲስ አበባ ላይ ሊወሰድ ነው የተባለው እርምጃ ውሎ አድሮ እራሱ ሕወሓትን ጠልፎ እንደሚጥለው ለማወቅ ብዙ ውስብስብ ጉዳዮችን ማሰብ አያስፈልግም።

ከእዚህ በታች አለምነህ ዋሴ ጉዳዩን አስመልክቶ የለቀቀውን ዜና ያዳምጡ።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...