ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, January 13, 2017

በጎንደር እና ጎጃም ሕዝብ ላይ በአዲስ መልክ የታወጀውን የሕወሓት የደም ማፍሰስ እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ የማይቃወም ኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያ ክፍል የህዝቡ ደም በእጁ ላይ እንዳለ ይወቅ! (የጉዳያችን ማሳሰቢያ)

ጉዳያችን / Gudayachn
www.gudayachn.com
=============================================================
በጎንደር የገጠር እና ከተማ ነዋሪ ሕዝብ ላይ ሕወሓት አዲስ እልቂት ለመፈፀም ሰራዊት እያስገባ ነው።ለኢሳት ዛሬ መለጫ የሰጡት የጎንደር ሕብረት ሰብሳቢ አቶ አበበ ንጋቱ የጎንደር ሕዝብን ደም ለማፍሰስ በ40 መኪና ተጭኖ ከተለያየ አቅጣጫ ወደ ጎንደር የተለያዩ መሬቶች ገብቷል። ይህ የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ታሪክ ባለቤት ከሆነው ክፍል ውስጥ አንዱ በሆኑት በጎንደር እና በጎጃም ላይ  የመዝመት እና የማጥፋት ዘመቻ ነው።

የኢትዮጵያውያን ደም በከንቱ ሲፈስ እንዳላዩ ሆኖ ማለፍ በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የሚገኝ ኢትዮጵያዊ ተግባር ሊሆን አይችልም።ጉዳዩ በዝምታም፣በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ መንገድ የሕዝቡ ደም ሲፈስ የተሳተፉ ሁሉ በእጃቸው ላይ የንፁሃን ደም እንዳለ ሊያውቁት ይገባል።ይህንን እልቂት ለማስቆም ከአዲስ አበባ እስከ ወለጋ፣ ከወለጋ እስከ አክሱም፣ከአክሱም እስከ ሞያሌ እና ጅጅጋ ያለ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በቸልታ ሊያልፈው አይገባም። ሕወሓት ስልጣኑን እንደሚያጣ ሲያውቅ የዘር ማጥፋት ዘመቻ በጎንደር እና ጎጃም ላይ እንደሚያውጅ ቀድሞም ይታወቅ ነበር።አሁን በአዲስ መልክ ሊፈፅመው እየተዘጋጀ ያለው የእልቂት ድግስ በመጪዋ ኢትዮጵያ ላይ ጥሎ የሚሄደው ጠባሳ ጥሎ የሚሄድ ታሪካዊ ስህተት ነው። በሌላ በኩል  እነኝህን አካባቢዎች ማጥፋት ኢትዮጵያ ካሏት ልዩ ልዩ አሻራዎች ውስጥ አንዱ የሆነውን    የማጥፋት ተግባር በሕወሓት እየተከናወነ እንደሆነ ማወቅ ይገባል።

ባጭሩ በጎንደር እና ጎጃም ላይ የተደገሰውን አዲስ የደም ማፍሰስ እና የዘር ማጥፋት የሕወሓት ዘመቻ በዝምታ መመልከት እና ሕወሓትን በሁሉም አቅጣጫ አለመቃወም በጎንደር እና ጎጃም ሕዝብ ደም ላይ እጅን መንከር ነው።


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።