ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, November 18, 2014

ኬንያ፣ቡክናፋሶ እና አዲስ አበባ በእዚህ ሳምንት (ከሶስት ደቂቃ ያነሰ አጭር የቪድዮ ዜና ጋር)

 ኬንያ 

ኬንያ አንዲት ወጣት ሚኒስከርት በመልበሷ በወንዶች የደረሰባት ጥቃት በመቃወም ትናንት ሰኞ  በሺህ የሚቆጠሩ የናይሮቢ ሴቶች፣ተማሪዎች ሰልፍ ወጡ። ሕግ ይስተካከል! አዲስ አበባ ላይ በአውሬ ለበስ  ወንዶች ጥቃት የደረሰባት ሃና ሕይወቷ አልፎ የአዲስ አበባ ወጣት ሕጉ ይሻሻል ብሎ አይጮህም።ነገ በእኔ ነው።

ቡክናፋሶ

የሃያ ሰባት ዓመት አምባገነንነት ለሌላ ተጨማሪ  ዓመታት በስልጣን ላይ ለመቀመጥ ፓርላማው ሕጉን እንዲቀይር ያደረጉት ፕሬዝንዳንትን በሁለት ቀን አብዮት አስወግዶ ዛሬ ወታደራዊ አመራርን በሲቪል አስተዳደር ቀየረ።ሀገሪቱ  በመጪው ዓመት የአሁኑ ጊዚያዊ ፕሬዝዳንት የማይሳተፉበት አዲስ ምርጫ ታደርጋለች።ጊዝያዊ ፕሬዝዳንት ዛሬ ቃለ መሃላ ፈፀሙ።

አዲስ አበባ

በመጪው እሁድ አዲስ አበባ ላይ ከአርባ ሺህ ሕዝብ የማይንስ የሚሳተፍበት ታላቁ እሩጫ መነሻ እና መድረሻውን ጃን ሜዳ አድርጎ ይደረጋል።ገበታው በያይነቱ ነው።ከኬንያው የባሰ ጥቃት እህቶቻችን ላይ ተፈፅሟል።ከቡኪናፋሶ የከፋ በጎሳ ላይ የተመሰረተ አምባገነንነት በኢትዮጵያ አናት ላይ እየጨፈረ ነው።አንድ እንቁላል 3 ብር ከ 50 ሳንቲም በሚሸጥባት አዲስ አበባ አፍ ለጉሞ መሮጥ በራሱ ጤነኝነት አይመስለኝም።ኬንያ እና ቡክናፋሶ ጥለውን ሄዱ። ከእዚህ በታች ያለውን 3 ደቂቃ የማይሞላ ዜና ይመልከቱ።



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።