Friday, September 6, 2013

ከሰላሳ ሺህ ቃላት በላይ የያዘ ኖርዌይኛ-በአማርኛ አዲስ መዝገበ ቃላት በገበያ ላይ ዋለ

አምስት መቶ ስልሳ ገፅ የያዘ ኖርዌይኛ በአማርኛ  መዝገበ ቃላት በአይነቱ ልዩ በሁለት ኢትዮጵያውያን ተዘጋጅቶ እና በኖርዌይ ትምህርት ሚኒስቴር ታትሞ በመፃህፍት መደብሮች በገበያ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።በኖርዌይ የብዙ ሀገሮች መዝገበ ቃላት (የሱማልኛን ጨምሮ) በኖርዌይኛ ተተርጉሞ መኖሩ ሲታወቅ የኢትዮጵያ ግን በእየመፃሕፍት መደብሮች አልፎ አልፎ ከሚታዩት  በቃላት ብዛታቸውም ሆነ በይዘታቸው እጅግ ትንንሾች እና የተወሰኑ ቃላትን ብቻ የያዙ ጥቂት የአማርኛ እና የትግሪኛ መዝገበ ቃላት ብቻ በመኖራቸው በብዙዎች ዘንድ ደረጃውን የጠበቀ የመዝገበ ቃላት አስፈላጊነት ጉዳይ ሲወሳ ነበር። 

ይህ ከሰላሳ ሺህ በላይ ቃላት መያዙ የተነገረለት መዝገበ ቃላት የተዘጋጀው በሁለት ኢትዮጵያውያን ማለትም በአቶ እንግዳ እሸት ታደሰ እና  በተባባሪያቸው አቶ አበበ ተፈራ ሲሆን እንደ አቶ እንግዳ እሸት ገለፃ መዝገበ ቃላቱን ለማዘጋጀት እና ደረጃውን የጠበቀ አድርጎ ለማውጣት  ሃያ አመታት እንደደከሙበት ለማወቅ ተችሏል። 

ኢትዮጵያውያን በሚኖሩበት ሀገር ሊሰሯቸው ከሚገባቸው ተግባራት ውስጥ ዋነኞቹ እንደዚህ አይነት ትውልድ ተሻጋሪ እና ለሀገር የሚጠቅሙ ስራዎች መሆን እንደሚገባ የኢትዮጵያውያኑን ሥራ በአብነት መጥቀስ ይቻላል።

በመጨረሻም መፅሐፉን በመስመር ላይ ( on line) ለማዘዝም ሆነ በአካል ወደ መደብር ሄደው  ለመጠየቅ የመፅሐፉን ኮድ (ISBN number 978-82-450-1360-3) መያዝ ጊዜ ይቆጥባል።



ጌታቸው በቀለ 
ኦስሎ 


1 comment:

Anonymous said...

Nice Job Gechiye.
berta.
thank you.

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...