ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, September 10, 2013

የ2005 ዓም የጉዳያችን ጡመራ ሁለት ምርጦች


የእኔ የ2005ዓም ምርጤ ማነው? ብዬ አሰብኩ።

ዘንድሮ ማንን አደነቅሁ? ብዬ እራሴ ለእራሴ ጠየቅሁት? ለአመታት ያጣነውን የሙያውን ስብዕና እያላበሱ ያሉ ሁለት ክቡራኔን አገኘሁ።የጋዜጠኛ ሙያ ስብዕናን።

ዳኛው እኔው መራጩ እራሴው። ምን ቀረ?
በ 2005 ዓም ብዙ መልካም የሰሩ ሰዎች ይኖራሉ። እኔ ግን ስለ እነኚህ ኢትዮጵያውያን ''የአመቱ ሰው'' ብላቸው ማን ከልካይ አለብኝ?

ማንነህ እና ነው አንተ የአመቱ ምርጥህን የምትመርጠው? ማለት አይቻልም።በጡመራ መድረክ(ብሎግ) ሁሉም ሰው ሃሳቡን በነፃ እንዲገልፅ የፈቀደው ህገ-ቴክኖሎጂ የእዚህ አይነቱን ጥያቄ አያስተናግድምና።

በ 2005 ዓም ብዙ ነገር አድንቄ ይሆናል።ሀገራቸውን ከልብ ከሚወዱ ውስጥ በሩቁ የተመለከትኩትን ግን እንዳደንቅ ይፈቀድልኝ።

ደግነቱ አያውቁኝ አላውቃቸው።የቴሌቭዥን መስኮት አገናኘን እንጂ።እኔ በመመልከት እነርሱ በማቅረብ። ሌላ የምሸልማቸው የለኝም።ያለችኝ ትንሿ የጡመራ መድረክ (ጉዳያችን ጡመራ) ነች።

እነኚህ ሁለት ምርጦቼ ስለሚከተሉት ሶስት ነገሮች የአመቱ ምርጥ ጋዜጠኞች መባል አለባቸው እላለሁ።

  •  ጋዜጠኝነትን ኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ትሕትናን እና ድፍረትን በአንድነት አላብሰውታል፣
  •  የሃገር መውደድ ከፊታቸው ይነበባል። የእውነት መደበቅ ደግሞ  ሲያበሳጫቸው ያስታውቅባቸዋል፣
  • በሚያቀርቡት ጥያቄ ሃብታምን በሀብቱ አያፍሩትም፣ጉልበተኛውን ስለጉልበቱ አይራሩለትም ተመልካች አዕምሮ ውስጥ ሊኖር ቢችል ያሉትን ጥያቄ ያቀርባሉ።

የኢሳት ጋዜጠኞች ሲሳይ አጌና  እና ደረጄ ደስታ የ 2005 ዓም ምርጥ የጋዜጠኝነት ብቃት በማሳየት ምርጦቼ ናቸው።

ጌታቸው በቀለ
ኦስሎ


ጋዜጠኛ ደረጄ ደስታ                                           




              ጋዜጠኛ   ሲሳይ አጌና



























1 comment:

Anonymous said...

Thank you. many agree with your preference.