ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, January 31, 2012

ኢሳት ( ኢትዮጵያ ሳትከፋ ትኑር)

''ተ ቦርን'' የሚለውን ስም ''ታዲያስ አዲስ'' በተባለው ሸገር ኤፍ ኤም ፕሮግራም ላይ የማያውቀው ያለ አልመስልህ አለኝ:: ''ተ ቦርን'' ቅጥል ስም ነው እንጂ ስሙ ተወልደ በየነ ይባላል:: በኪነቱ አለም በ ሃያሲነትም ሆነ በሙዚቃ ግጥም ቅንብር  ስሙ ይወሳል:: አንድ ጊዚ እንዲያውም በሃገራችን ያሉትን ዘፈኖች ከ ባእዳን ዘፈን ዚማ የተቀዱትን እየለየ አሰምቶን ጉድ አጀብ አስብሎ ነበር::
ለጠቅላላ እውቀት እንዲሆናችሁ ''ተ ቦርን'' ማለትም ተወልደ በየነ የ  ታዋቂው አርቲስት እና አክቲቭስትታማኝ በየነ የ ስጋ ወንድም መሆኑን ሳትነግረን እንዳትሉ ነገርኩዋችሁ አሁን::


ባለፈው ሳምንት በኢሳት  ራድዮ ከ ምድረ አሚሪካ ሃሳቦቹን ለ ወገኑ የ ኢትዮጵያ ህዝብ ሲያካፍል አመሸ:: እናም ብዙ ሃሳቦች ያሉት ወጣት ነው::

በ እዚሁ ኢሳት ( ትርጉሙ ኢትዮጵያ ሳትከፋ ትኑር ብየዋለሁ) ራድዮ ላይ ቀርቦ ከነገረን ቀልድ ላወጋችሁ ነው::
'' አንድ ቀን ጠቅላይ ሚንስትሩ ከልጃችው እና ባለቢታችው ጋር በአይሮፕላን ይጓዛሉ እና በጉዞ መሃል አንድ መቶ ብር አንስቸ ወደ ምድር ልወርውርና አንድ ኢትዮጵያዊ ላስደስት ይላሉ:: ባለቢታችው ታድያ ለምን ሃምሳ ሃምሳ ብር አርገህ ሁለት ኢትዮጵያዊ አታስደስትም አለች ልጂት ደሞ ተነሳችና ለምን ብሩ አስር አስር ተዘርዝሮ አስር ወገናችን አይደሰትም? አለች በ እዚህ ጊዚ የ አይሮፕላኑ አብራሪ ካፒቲን ዘወር አለና ለምን እራስዎ ወርደው ሰማንያ ሚልዮን ህዝብ አይደሰትም?'' አላቸው'' ብሎ አሳቀን
''ተ ቦርን'' ስለ ሃገረ ኢትዮጵያ ገና ብዙ የምነግራችሁ አለ ከ ሆዴ ያለ ስላለ ገና አለ ገና...እያልን ከ ኢሳት ( ኢትዮጵያ ሳትከፋ ትኑር) የ 24 ሰአት ራድዮ እና ቴሊቭዥን መስኮት ብቅ እንደሚል ቃል ገብቶልናል::''ታዲያስ አዲስ'' ''ተ ቦርን'' (ኢሳት-ኢትዮጵያ ሳትከፋ ትኑር)......አበቃሁ::

4 comments:

Anonymous said...

weyne TE BORNYE HEDKBN?

Anonymous said...

ESAT we love you

Anonymous said...

Thanks Gech

Anonymous said...

yigermal weyne TE BORNYE HEDKIBN?