Saturday, December 15, 2012

ኳታር በ ምስራቅ አፍሪካ ጉዳይ



አቶ ኢሳያስ ለድርድር ኳታርን ሸምግይኝ ማለታቸውን ''አዋተ''የተሰኘውን ድህረ ገፅ አስታውቋል። እርግጥ ነው አቶ ሃይለማርያም ባለፈው ለአልጀዚራ ሲናገሩ ''አቶ መለስ ከ ሃምሳ ጊዜ በላይ ጠይቀዋል እኔም አሁኑኑ አስመራ ሄጄ ለመደራደር እቻላለሁ'' ማለታቸው ይታወሳል። ለሰላም ለመነጋገር በኳታር በኩል ከመዞር እንደ እኔ እንደ እኔ በደብረ ዳሞ በኩል ተቀታጥሮ አንዳፍታ መወያየት ይቀል ነበር። ኳታር '' አልጀዚራ'' የተሰኘው የሌቭዥን ጣብያ ማዕከል ብቻ ሳይሆን ባላት የ ተፈጥሮ ጋዝ እና ነዳጅ ሀብት በ 2009 ከተባበሩት አረብ እምሬት ቀጥላ በመካከለኛው ምስራቅ ካሉት ሃገራት ውስጥ በ ተባበሩት መንግሥታት የ '' ሰው ልማት ሰንጠረዥ'' (Human development Index) የሁለተኘትን ደረጃ ይዛለች።

''ትንሽ ሀገር ትልቅ ችግር?'' (small country but big problem)

የኳታርን በተለይ በተለይ በአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ላይ ዘው ብላ መግባቷን ያዩ እና  ሌሎች ሀገሮች ጉዳይ ላይ ደግሞ በዜና ማሰራቻዎ ማራገቧን የተመለከቱ የአካባቢው አጥኚዎች ''ትንሽ ሀገር ግን ትልቅ ችግር'' ብለው ይጠሯታል።የሀገሪቱ ያለፈ ታሪክ ላይ ትንሽ ስእል ለመስት:-

·  እ.አ.አ  1783 እስከ 1868 ባህራ አስተዳደር ስር፣
·  እ.አ.አ  1871 እስከ 1916  ኦቶማን ኢምፓየር ስር፣
·  እ.አ.አ  1916 እስከ 1971  እንግሊዝ ስር ተዳድራለች።

ከሁለተኛው አለም ርነት መጠናቀቅ ተከትሎ ሀገሪቱ  እንግሊዝ ቅኝ የነበሩ ሃገራት ነፃነታ ውን ሲያገኙ እንግሊዝም  ፖለቲካ ስልጣን ለመስጠት  ሶስት አመት ጊዜ አስቀምጣ ስለነበር ኳታርም  ፈረንጆ አቆጣጠር  1968ዓም  ባህሬን ጋር  ፈድሬሽን እንድትዋሃድ አደረገቻት።  መጨረሻ አሁንም  አውሮፓውያን አቆጣጠር  መስከረም 3 ቀን 1971 ዓም ሙሉ ነፃነቷን አገኘች። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን  አለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ  ማደራደር አቅሟን ለማጎልበት ጥረት አድርግላች።  ምዕራብ ሳሃራ ግጭት ፣ብ የመን ግጭት እና  ፍልስተሞቹ ''ፋታህ'' እና ''ሐማስ'' ምካከል ለመሸምገል ሞክራለች።

የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ እና ኳታር

ኳታር  አፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ላይ መግባት የጀመረችው  ደርግ ዘመነ መንግስት ነበር። ሻብያ በኢርትራ  ሲዋጋ ስንቅ እና ትጥቅ አቀባይ ከሆኑት ሃገራት ውስጥ ብቻ ሳይሆን  ቀንደኛ  ድርጅቱን አባላት በማስጠለል እና  መንቀሳቀሻ ፓስፖርት በመስጠትም ትታወቅ ነበር። ይሄው ግንኙነት  ደርግ መውደቅ ጋር የተሻሻለ መልክ የያዘ ቢመስልም ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ተከትሎ የመሻከሩ ደረጃ ብሶበት  አውሮፓውያን አቆጣጠር  2008 ዓም ተመልሶ  ኢትዮጵያ እና  ኳታር ዲፕሎማሲ ግንኙነት መልሶ ተቋረጠ።  ቅርቡ  አቶ መለስ እረፍት ተከትሎ ባለፈው ጥቅምት 2012 ዓም ነው ኳታር  ዲፕሎማሲ ግንኙነቷን  ኢትዮጵያ ጋር ያደሰችው።


ኳታር  ሱዳን እና  ኤርትራ መሃከል ያለውን በጫፍ ያለ የሚባልለትን ግንኙነት  በመያዝም ትታወቃለች። በሁለቱ መሬቶች መሃከል ያለውን የድንበር ችግር ለመግታት የድንበር ከተሞቹ ላይ የኢንዱስትሪ ማዕከል ልመስርትላችሁ ብሎ ከመጠየቅ ባለፈ በገንዘቧ የሁለቱን ሃገራት የሚያገናኝ የአስፋልት መንገድ ሰርታ ባለፈው አመት ጥቅምት ወር ላይ የኳታር መሪ ኤሚር  ሐመድ አል ታኒ፣የ ሱዳኑ አልበሺር እና  ኤርትራው ኢሳያስ በተገኙበት አስመርቃለች። በምረቃውም ላይ  ሱዳኑ አልበሺር ኤርትራ  እሳቸው ላይ  ዓለም አቀፉ ፍርድቤት  ቆረጠውን  መያዥያ ሰነድ ወደጎን በማለት ያስተናገደቻቸው ሀገር መሆኗን ጠቅሰው ወደፊትም ነፃ  ድንበር ክልል እንዲኖር እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። ይህን ይበሉ እን  ሁለቱን መሬቶች ግጭት  ኳታር  ገንዘብ ይል እንዲገታ መደረጉን እና  ጊዜ ቦንብ መሆኑን ግን ለማውሳት አልበሺርም ሆኑ ኢሳያስ አልደፈሩም።

የኳታር ኢሚር ፣አልበሽር እና ኢሳያስ ኳታር ያሰራችውን መንገድ ሲመርቁ


የኳታር የ ድርድር ጥያ ቀደም ብሎ የጠየቀ የነበረ ቢሆንም በ አቶ ኢሳያስ የግል በጎ ፈቅድ ብቻ የሚመራው የኤርትራ አስተዳደር በ አንድ በኩል የመለስን መሞት ተከትሎ የሚመጣውን ለውጥ ስተባብቅ በ ሌላ በኩል ደግሞ በ ኢትዮጵያ በኩል ጫፍ የያዙ የ ህዋሀት አመራሮች ሲጎትቱት የቆየ ጉዳይ ነበር። አሁን ግን ሁለቱም ለድርድር የሚቀርቡ ከሆነ ስለ ሚከተሉት ምክንያቶች ብቻ እንጂ ለውጤት ሁለቱም እንደማይተጉ ግን ለመረዳት ሊቅ መሆን አያስፈልግም። ለድርድር እንዲቅርቡ ያደረጋቸው ምክንያት የመጀመርያው በ ኤርትራ በኩል እና በ ኢትዮጵያ በኩል ያለው የውስጥ ቅራኔ ከፍተኛ ደረጃ ስለደረሰ እና ለ ቅራኔው አቅጣጫ ማስቀየርያ ትልቁ የሀገር ውስጣቸውንም ሆነ አካባብያዊ ብሎም አለምአቀፍ ፖለቲካን የማብረጃ ስልት አድርገው ስላዩት ብቻ ነው። ኤርትራ የ ኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች ስልጠና ከምስጠት አልፎ አስከ ማስታጠቅ ድረስ እየሰራች እንደሆነ አቶ መለስ ብዙ ጊዜ ተናግረዋል። ኢትዮጵያም ከፍተኛ ባለስልጣናቷ ሳይቀሩ የተገኙበት የ አቶ ኢሳያስ ተቃዋሚዎችን አለማቀፍ ስብሰባ ከማስተናገድ አልፋ ''በ አረብ ሳተላይት'' በኩል ''ዳሽ ኤርትራ'' የተሰኘ የ ቴሌቭዥን ፕሮግራም ከ ምሽቱ አራት ሰዓት ጀምሮ ዘወትር ማስተላለፍዋ እና የ ኤርትራ ቴሌቭዥን የደበቃቸውን የሃገር ውስጥ ክስተቶች ይፋ መሆናቸው በ እረጅም ጊዜ ተፅኖ መፍጠሩ አልቀረም። ከሁሉም ግን ኤርትራ ከ ዓለም ሕብረተሰብ ከ ሚድያውም በመጥፋቷ ትንሽ ለ ዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ አርስት መሆንም አስባ ይሆናል።የምሰመርበት ግን ሁለቱም ሃገራት ውስጣዊ ችግሮቻቸውን ማስታገሻ እና ማስቀየሻ የምትመዘዘውን የ ተለመደች ካርድ መምዘዛቸው ብቻ ነው።

ከሁሉም ግን አሳዛኙ ክስተት የሁለቱ ሃገራት ጉዳይ በ አቶ ሃይለማርያም እና አቶ ኢሳያስ እጅ ላይሆን የመቻሉ ጉዳይ ነው። ጉዳዩ እጅግ ግሎ ውይይት የሚደረግበት እና የሚወሰነው በ ድብቅ በር በ ሁለቱ የ ጦር አለቆች ዘንድ ነው። በ ሁለቱም የ ጦር ሰራዊት አዛዦች ዘንድ ከ ብሔራዊ እና ስትራተጃው አስተሳሰብ ይልቅ ክልላዊ እና የ ትውልድ ቦታ ቅድምያ ስለሚሰጠው እልህ እና ተደፈርኩ ባይነት የጎላበት ስሜት ብዙውን ጊዜ የ ፕሬዝዳንቱንም ሆነ የ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሚና ያኮስሰዋል። በመሆኑም ይህን የሚያውቁት አቶ ኢሳያስ ባለፈው ለ አልጀዚራ ቴሌቪዥን አቶ ሃይለማርያም የሰጡት '' አስመራም ቢሆን ሄጄ እደራደራለሁ '' የሚለው ንግግር በ ህዋሀት የጦር አበጋዞች ዘንድ ምን ያህል ንዴት እንደፈጠረ እና ይህ ልዩነት ደግሞ ''ኳታርን አደራድርኝ ብላትማ የትየለሌ ይደርሳል'' አሉና አቶ ኢሳያስ ይሄው ''ያለቅድመ ሁኔታ እንደራደር'' አሉ ተባለ። ''እውነትና ንጋት እያደር'' እንደሚባለው በ ሺህ የሚቆጠረው የ ኤርትራ ወጣት በሺ ከሚቆጠረው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ እና አህቱ ጋር በ የመን በሱዳን በ እግሩ እየሄደ ይንከራተታል። ለህዝባቸውም ሆነ ለ እራሳቸውም ያልሆኑት መሪዎች ግን አንዴ ከ ኳታር አንዴ ከ ዱባይ እያሉ በ ህዝቡ ይነግዳሉ።
                       ከ ኢትዮጵያም ሆነ ከ ኤርትራ ስደተኛው ሃገሩን ትቶ መሄዱን ቀጥሏል።




Monday, December 10, 2012

የ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የ ዕርቅ ጉባኤ በተመለከተ ያለኝ ሃሳብ (የ ዳላሱ ንግግር ማብቃቱ እንደተነገረ)


ኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሃገር ውስጥ ውጭ የሚገገኙ አባቶች እርቅ ጉባዔ አሜሪካ ዳላስ ላይ ማድረጋቸው እና በትናንትናው እለት መጪው ወር ሎስ አንጀለስ ላይ ተቀጣጥረው መለያየታቸውን ደጀ ሰላም የተሰኘው ብሎግ ዛሬ አስታውቋል።

እዚህ ጉባዔ ምንም እንኳን የተፈለገውን ያህል ውጤት ባይገኝም የነገን እርቀ ሰላሙን አካሂያድ በደንብ መጤን ያለበት መሆኑን ግን የሚያመላክት ይመስለኛል። በመሆኑም ሁኔታዎች ካሁኑ መስተካከል ያለባቸው መሆኑን ሁሉም ወገኖች ሊያጤኑት የሚገባ ይመስለኛል::


 ዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አባቶች አቀባበል ተድርጎላቸው (ፎቶ ከ ደጀ ሰላም ብሎግ)

የ አስታራቂው ኮሚቴ በተመለከተ


አስታራቂው ኮሚቴ እስካሁን ያሳየው ትጋት የሚያስመሰግነው ነው። ሆኖም ግን ምንም እንኳን ዝርዝር ጉዳዮችን ባላውቅም ሰው ሃይል ጉዳይ መስፋት ያለበት እና ቤተ ክርስቲያኒቱ ካላት የሰው ሃይል አንጻር በመጪዎቹ ውይይቶች ምዕመናንን ፍላጎት ቤተክርስቲያኒቱን ደረጃ በሚመጥን መልክ ምዕመናን ሌሎች ቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት የሚያከብሯቸው ምዕመናን መካተት ያለባቸው ይመስለኛል።ይህም አስታራቂ ኮሚቴው አባቶችን ንግ ግር ለመስማት እራሱ ትልቅ ቤተክርስቲያንን ሃላፊነት የሚጠይቅ እና ቤተ ክርስቲያኒቱ ተጻራሪዎች አሳልፎ የማይሰጥ መሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ነው። ምክንያቱም ንግ ግር ነውና አባቶች ውይይቱ ወቅት ከድሮ የነበሩ ታሪኮችን፣ድርጊቶችን በስሜት ሆነው ማውራታቸው አይቀርም። በመሆኑም አሁንም ለእዚህ ደረጃ የበቃ የሰው ሃይል አስታራቂ ኮሚቴው ውስጥ መጨመር አለበት። ምናልባትም አስታራቂ ኮሚቴውን የሰው ሃይል እንደገና ማየትም ሊያስፈልግ ይችላል።እዚህ ላይ ችግሩን ያልፈቱት አባቶች ሳሉ ለምን አስታራቂ ኮሚቴው ላይ ይተኮራል የሚሉ ሊኖሩ ይችላሉ። ነገር ግን አሁን በኋላ የሚኖረው ውይይት ምዕመናንንም ጥያቄ የያዘ፤ አዲስ የተሻለ ሃሳብ የሚያቀርብ እና ሃገር ውስጥ ከመንግስት ጀምሮ ውጭ እስካሉት ተጽኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጭምር አስፈላጊ ሲሆን የሚያናግር ብሎም ድብቅብቅ አስራር ተላቆ እርቅ መርሃግብሩን አቅድ ሁሉ ህዝቡ ጋር ተወያይቶ የሚሄድ ጉዳዩንም ባለቤቱ ምዕመኑ የሚያሳውቅ መሆን አለበት። ይህ ሲሆን ሁሉንም እረፉ ቤተ ክርስቲያን በላይ ሆነ አገልጋይ ሊኖር አይችልም የሚል ወደመፍትሔው የሚመራ መንገድ መታየት ይጀምራል።

በእርግጥ ሃይማኖት ነው ችግር መፍትሔ የሚሰጠው እግዚያብሔር ነው።ማወቅ ያለብን ግን እግዚያብሔር ተጣሉ አለማለቱን ነው። ሁሉም በላይ ግን ትልቅ ጥንቃቄ የሚሻው እና ምዕመናን የሚጠበቀው የሚመስለኝ ሁሉንም አባቶች ለመውቀስ አለመቸኮል ነው። የችግሩ አነሳስ ባህሪ፤ሂደቱ አሁን ያለበት ሁኔታ ሃገራችን ፖለቲካዊ ገጽታ ጋር የመያያዙ ክስተት አባቶች ቶሎ ወደ ውሳኔ እንዳይሄዱ ቸግሯቸዋል ብለን ብንረዳ እራሳችንን እያታለልን ያለን አይመስለኝም።ለችግሩ መንስዔዎች ውስጥ እኛ ምዕመናን ድርሻ የሌለ እንዳይመስለን።አባቶቻችንን( ውጭም ሆነ ሃገር ቤት ያሉትን) እንዴት ከዚህ ውስብስብ ችግር እንዲወጡ እንርዳቸው ብሎ ማሰብ የእውነተኛ ልጅነት መለያ ነው። አባቶች ተፈትነዋል ፈተናውን ግን እነርሱ ብቻ ናቸው ያመጡት ማለት አይቻልምና።
ለምን ሎስ አንጀለስ?
አሁኑ ዕርቅ ጉባዔ ዳላስ ሲደረግ ሁለቱም አባቶች በጎ ፈቃድ የነበረ መሆኑ ቀደም ብሎ ተገልጾ ነበር። ሎስ አንጀለስ ላይ በመጪው ወር ይደረጋል ሲባል ግን ለምን ሎስ አንጀለስ? አልኩኝ። ሎስ አንጀለስ ለማደራደር አትበቃም ለማለት ሳይሆን።ጸሎት እንኳን ከጀመሩበት ቦታ ጸንተው ሲፈጽሙት በጎ ነው ይላሉ አባቶች። አስታራቂው ኮሚቴ ነው የመረጣት ሎስ አንጀለስን? ወይስ ቤተክርስቲያን እርቅ ጉባዔ ሁሉንም አሜሪካ ከተማ ማዳረስ አለበት?

ይህችን አነስተኛ ጽሁፍ ለመደምደም ግን አሁንም አስታራቂ ኮሚቴው መሰረተ ሰፊ ፤አቅም ያላቸው ሰዎች (አቅም ሰጪ አምላክ መሆኑ ሳይረሳ)ማካተት እና በኮሚቴው ውስጥ አቅም በታች ያሉ ካሉ በስራው አጋዥነት መድቦ ሌሎች ስራዎችን እንዲያከናውኑ ማድረግ ተገቢ ይመስለኛል። ከሁሉም ከሁሉም ግን እራሱ አነሳሽነት የተነሳው ኮሚቴ ተመስግኖ ምዕመናን ቤተክርስቲያኒቱ ባለድርሻዎቿ (ርስት ወራሽ ናቸና)የተወከሉበት ሰፋ፣ጠንከር እና ተጠያቂነት ያለው አስታራቂ ኮሚቴ አስፈላጊ ነው።

አበቃሁ
ጌታቸው
ኦስሎ


Sunday, December 9, 2012

መጠይቅ

''ከ ወቅቱ የ ኢትዮዽያ ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ሁኔታ አንጻር የሃገራችን መሰረታዊ ችግር የሚመነጨው ከየት ነው ብለው ያስባሉ?''

 
  •    የ የኢህአዲግ የ ፖሊሲ መሰረት የሆነው ብሔርን እና ቋንቋን መሰረት ያደረገ አስተዳደራዊ ዘይቤ?
  •   የ የኢህአዲግ ህገ መንግስቱን አለማክበር?
  •  
  •  ከ ኢትዮዽያ ስትራቴጃዊ አቀማመጥ የተነሳ ሃገራችንን ለማዳከም ያለመ የ ውጭ ሴራ?
  •  
  • ከቀደመው የ ሃገራችን ታሪክ?
 
 
ከ ብሎጉ ገፅ በ ግራ ጎን በኩል የተቀመጠውን መጠይቅ ከ ስር ከተሰጡት ምርጫዎች በ አንዱ ወይንም ከእዚያ በላይ ምክንያት ናቸው ካሏቸው ውስጥ  በመምረጥ ሃሳብዎን ይግለፁ።
ከ ምስጋና ጋር።
 

Friday, December 7, 2012

“መለስ ከመቃብራቸው እየገዙ ነው። ግን ይህ እስከመቼ ይዘልቅ ይሆን?..''መለስ በሌለበት ህዋሃት አንጎሉን አጥቷል'' - ሬኔ ለፎንት (ቃለ ምልልሱን ያዳምጡ)

ሬኔ ለፎንት በ 1960ዎቹ ጀምሮ ከ ሳሃራ በታች በተለይ ስለ አፍሪካ ቀንድ በመፃፍ የታወቁ ናቸው። በ እዚሁ የ አፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ለ ታዋቂዎቹ የ ፈረንሳይ ጋዜጦች ''ለሞንድ''(Le Monde)፣''ለሞንድ ዲፕሎማቲክ'' (Le Monde diplomatique) እና ለ  ''ኖቭል ኦብሰርቫቱር ''(Le Nouvel Observateur) በ ሪፖርተርነት ሰርተዋል። በ 1975 ዓም ''Ethiopia: an heretical revolution'' የተሰኘ መፅሐፍ ፅፈዋል።
መፅሐፉን በ እዚህ ሊንክ ከ ''አማዞን'' ማዘዝ ይችላሉ።
(http://books.google.no/books?vid=ISBN0862321549&redir_esc=y)

ሬኔ ለፎንት ኢትዮጵያን በተመለከተ ለ አሜሪካ ድምፅ ራድዮ የ አማርኛው አገልግሎት  በ እዚህ ሳምንት  ጥልቅ ትንተና ሰጥተዋል።በ ኢትዮጵያ ጉዳይ ከ ሰላሳ አመት ሲያጠና የነበረ ሰው የሚናገራቸው ነገሮችን ማቃለል የሚቻል አይመስለኝም።ሬኔ ለፎንት በ እዚህ መግለጫቸው ''መለስ በሌለበት ህዋሃት አንጎሉን አጥቷል'' ብለዋል ።ስለ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ሹመት፣ስለ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፣ስለ መጪው የ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ወዘተ አንስተዋል።
 ከእዚህ: በታች ያለውን ሊንክተጭነው ቃለምልልሱን:ያዳምጡ።(ሁለቱን ቃለመጠይቆች ለማዳመጥ ሊንኩን ከከፈቱ በኋላ  ማጫወቻዎች በተራ ይጫኑ) :-

ክፍልአንድ
 http://amharic.voanews.com/content/meles-rules-from-beyond-the-grave-part-1-12-04-12/1558576.html

ክፍል ሁለት 
http://amharic.voanews.com/content/rene-lefort-voa-peter-heinlein-part-2/1559339.html

 


Tuesday, December 4, 2012

''እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመበት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ '' ሐዋርያት ሥራ 20፣28

ሀገር ውስጥ ያሉት እና ውጭ ያሉ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አባቶች መካከል እዚህ በያዝነው ወር ውስጥ እርቅ ውይይትበ ደቡባዊቷ የ አሜሪካ ግዛት በ ቴክሳስ ዳላስ  ይደረጋል። ምእመናን እጅግ ጉጉት እየጠበቁት ያለ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የምትሄድበትን መንገድ የሚያመላክት ወሳኝ ውይይትም ነው። እኔም አባቶቻችን ውይይት እንደ ቤተክርስቲያኒቱ ልጅነት ምን መጠበቅ አለብን? ብዬ ሳወጣ ሳወርድ ቆየሁ። እናም ውይይቱ ውጤት እነኚህ ነጥቦች ባያንስብን ብዬ ተመኘሁ።

1 / '' ሁለት ሲኖዶስ'' ወደ አንድ ሲኖዶስ የሚያመጣ

2 / እውነተኛ ቤተክርስቲያንን አንድነት የሚያሳይ እና

3/ ሁሉም ያለፈውን እረስቶ ለነገዋ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገት  የሚተጋበት እንዲሆን

አንድ ግን መርሳት የሌለብን ነገር አለ።የ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሀገሪቱ አሻራ እንደመሆኗ ሀገራችን የነገ ሁለንተናዊ እሷነቷ ትልቅ ተፅኖ ያለው መሆኑን መዘንጋት የለብንም። እዚህም ነው አባቶችን መጪ ውይይት ኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ በጎ ምኞት የሚጠብቁትን ያህል ኢትዮጵያ ላይ ካላቸው የጠላትነት ስሜት ይህን ውይይት በጎ ፍሬ እንዳያፈራ ተግተው የሚሰሩ መኖራቸውን መዘንጋት የሌለብን።

ምእመናንም የትኛውም አይነት ፖለቲካዊ፣ፍልስፍናዊ፣ወዘተ አስተያያት ቢኖረን እዚህ ውይይት መርሃግብር ላይ ግን አንዳች ልዩነት ሊታይ አይገባም። ሁሉም እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንደ አንድ ልብ መካሪ ሆኖ ሁሉንም አባቶች ቤተክርስቲያንቱን አንድነት ላይ እንዲተጉ፣ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መሆናቸውን በማስገንዘብ ሊያበረታቷቸው ይገባል።

''እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመበት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ እኔ በኋላ ለመንጋይቱ የማይራሩ ነጣቂዎች ተኩላዎች እንደሚመጡ እኔ አውቃለሁ '' ሐዋርያት ሥራ 2028-30 የሚለው ቅዱስ ቃል ዛሬም ሕያው ነው እና።

ሊቀ ሊቃውንት አለቃ አያለው ታምሩ አንድ ወቅት ያስተማሩት ትምህርት እዚህ በታች ያዳምጡ።

ቸር ወሬ ያሰማን
ጌታቸው
ኦስሎ


 

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...