Friday, March 16, 2012

የ ኤርትራ ጉዳይ ና የ ሃያ አንደኛው ክ/ዘመን ልጆች አስተሳሰብ


በ ካርታ ጫወጣ ጎበዝ አደለሁም። ግን ጆከር የተባለች ካርታ መኖሯን አውቃለሁ።ጆከር ካርታ በ ሁሉም ቦታ ስለምትገባ በ ካርታ ጫወታ ጆከር የደረሰው ሰው የማሸነፍ እድል ስላለው ፊቱ በ ፈገግታ ይሞላል።
  የ አትዮጵያ ና የ ኤርትራ  ጉዳይን መሪዎቻችን   የ ፖለቲካ መጫወቻ ''ጆከር''  ካርድ  ካደረጉት  ቆዩ።  ፕሬዝዳንት ኢሳያስም ሆኑ ጠቅላይ ሚ/ር  መለስ ይችን ''ጆከር'' የተባለችውን የ ካርታ ካርድ በየሀገራቸው ይጫወቱበታል። በስልጣን ላይ ለመቆየት ይችን የ ኢትዮጵያ ና ኤርትራ ካርድ ትመዘዛለች፣ትርገበግባለች፣ትውለበለባለች፣በ ንግግር ላይ ጣል ትደረጋለች፣አስፈላጊ ሲሆን ደሞ ወደ ፋይል ክፍል ትገባና ስትጠራ የ አራዳ ልጅ  ''ከች በ ኮረኮንች'' አንደሚለው ''አንደገና ጆከር አንደገና'' ተብላ ትመዘዛለች።

የ ሃያአንደኛው ክፍለ ዘመን ልጆች  አዲሱ አስተሳሰብ

በ ሃያኛው ክ/ዘመን አጋማሽ የተነሳ የ ኤርትራ ጉዳይ ይሄው  እስከ ትናንትና ምሽት ድረስ ካርዱ እየተመዘዘ በሰው ሕይወት መቀለዱ ቀጥሏል። ይህን ችግር የፈጠረው ትውልድ ወደድንም ጠላንም እያለፈ ነው። በእናታቸው  ከ እንደርታ (ትግራይ) የሚወለዱት ፕሬዝዳንት  ኢሳያስም ሆኑ በ እናታቸው ከ ዓዲቇላ(ኤርትራ) የሚወለዱት ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ ለምን የ ጆከሯን ካርታ በየጊዜው  እየመዘዙ ሕዝቡን እንደምያሰቃዩት የሁሉም ሰው ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው ።
አንድ ነገር ግን መገንዘብ ይቻላል ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ህዝቡ የ ፖለቲከኞችን ልፈፋ ወደጎን ትቶ ነገሮችን የምያጠናበት ጊዜ ላይ መድረሱን ማንም ልብ ያለው ያለ አይመስልም። ኢሳያስም ሆኑ መለስ ካለ አንዳች ''ሃይ'' ባይ በ ፈለጉት መንገድ ላለፉት ሃያ አመታት የመሩት ሀገር ዛሬ ላይ ሲመለከቱት ብዙ ታሪካዊ ስህተቶች መኖራቸውን አፋቸው ባይናገረው ህሊናቸው ይፈርደዋል።ሁለቱም  ባለፉት ሃያ አመታት በታሪክ ታይቶ ያልታወቀ ስደተኛ በመላው ዓለም ማፍራታቸው  ቢያንስ  ለ ህዝቡ ያልሰሩት አልያም ያጎደሉት  ብዙ ሥራ መኖሩን ካልነገራቸው ጉድ  ነው።
አዎን! በ አልፈው ታሪካችን በጎ ዘመን የመኖሩን ያህል የ ፈተና ዘመን አልነበርም ማለት አይቻልም። ግን ቀይ ሽብር  አስመራ ላይ ሲሰማ አዲስ አበባም  በተመሳሳይ መንገድ ትታመስ ነበር። በየዘመኑ የነበሩ ፈተናዎች   በታሪክ አጋጣሚዎች የ ጦርነት አውድማ ያልሆኑ ቦታዎች ቢኖሩም መከራው ግን ያልጎበኘው ቤት አለ ማለት  ይከብዳል። ከዚህ ሁሉ በላይ ግን አንድ ደስ የሚል ሁሉንም የሚያስማማ ነጥብ አለ ። ይሄውም   እንደ ሕዝብ ተነስቶ  ሕዝብ በ ሕዝብ ላይ የሰራው በደል አለ ማለት ታሪካዊ ሂደቱን ና ክስተቱን አለማጠን ብቻ ነው ሳይሆን ተራ የ ፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ከመሆን የሚያልፍ አለመሆኑን ሁሉም መረዳቱ ነው። አሁን ቆም ብሎ የሚያስብ ትውልድ  ይመጣ ዘንድ መስራት አስፈላጊ ነው። ብዙዎች የተዘጋ ታሪክ የሚመስላቸው ግን ፖለቲካ፣ምጣኔ ሃብታዊ ትስስር፣ባህል፣ሃይማኖት፣ጆግራፍያዊ አቀማመጥ ወዘተ የ ሕዝቡን ችግር ከ ኢሳያሳዊ  ና መለሳዊ የ መለያየት ፖሊሲ በዘለለ ማሰብን የግድ ይላል።



Wednesday, February 29, 2012

በ ታሪክ ''ጢቢ ጢቢ'' መጫወት እና መዘዙ -የአድዋ ድል/ victory of Adwa.


አሜሪካኖቹ ስለ ሃገራቸው ቀደም ስላሉት አመታት ሲናገሩ(ስለ ሁለት መቶ አመት ታሪክ ቢሆንም) የሚጠቀሙበት አንዲት ብሂል አለቻቸው።'' መስራች አባቶቻችን'' የምትል።ስለ ህገ መንግስታቸውም ሆነ ስለ የነፃነት ቀን ሲያወሱ ''መስራች አባቶቻችን'' የምትለው ቃል አትለያቸውም።አውሮፓውያንም ተመሳሳይ ሁኔታ ይጋራሉ።ህገ መንግስታቸው ከረቀቀ  ከመቶ ዓመታት  በላይ የሆናቸው በየዘመኑ አንዳንድ ማሻሻያ ከማድረግ በላይ መሰረቱን ሳያናጉት ይሄው ዛሬም አሉ።ለዚህም ሳይሆን አይቀርም ብዙዎች የአውሮፓ ሃገራት ምክር ቤቶች የመጀመርያውን ምክር ቤት ወይንም ፓርላማ መስራችዋን ሀገር እንግሊዝን ጨምሮ ስፍራቸውን ሳይቀይሩ የመስራች አባቶቻቸውን በማሰብ ቀደምቶቻቸው በሰሩት ህንፃዎች አሁን ድረስ የሚገለገሉት ።የካቲት 23/2004 ዓም (ማርች 2 /2012) የዓድዋ ድል አንድ መቶ አስራ ስድስተኛ ዓመቱ ታስቦ ይውላል። ዘንድሮ ደግሞ ብዙ ወጣቶች ታሪኩ በሚገባ ለትውልድ መተላለፍ አለበት ብለው ከሃገር ውጭ ባሉ ከተሞች እንደሚከበር እይተወሳ ነው።ጥሩ ጅማሮ ነው።በርቱ ማለት ደግሞ ጤናማ ና ኃላፊነት የሚሰማው ሰው ሁሉ  አስተሳሰብ ነው።
ቅድመ  የ ዓድዋ ድል  (1885 እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር)
እንደ  አውሮፓውያኑ አቆጣጠር የካቲት 16 /1885 ጀርመን በርሊን ከተማ በሚገኘው ውብ በሆነው የ ሀገሪቱ ቻንስለር ቬን ቢስማርክ ባለስልጣን መኖርያ ህንፃ ሳሎን ፌሽታ በ ፌሽታ ሆኗል።ሶስት ወር ሙሉ አሰልቺ ውይይት የተደረገበት ዋና ዋናዎቹ የ አውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ተሰብስበው '' አንተ ይሄን ያዝ አንተ በእዚህ ውረድ''ተባብለው የ አፍሪካ ካርታ እንደምግብ በመካከላቸው ተዘርግቶ ከወታደራዊ ዘመቻ በፊት አፍሪካን የተከፋፈሉባት ቀን ነበረች። በ እዚህ ስብሰባ ከ 80 በ መቶ በላይ የ አፍሪካ መሬት በ ሃሳብ መስመር እያሰመሩ ተከፋፈሉት። የ በርልኑ ''General act of Berlin conference '' በ ታሪክ ባብዛኛው የሚታወቀው '' The division of Africa '' ወይንም ''scramble of Africa'' (አፍሪካን የ መቀራመት ጉባኤ) ተብሎ ነው ።በ እዚህ ጉባኤ ላይ ጀርመን፣ኦስትሮ-ሀንጋሪ፣ቤልጅየም፣ደንማርክ፣ፈረንሳይ፣ታላቅዋ ብሪታንያ፣ጣልያን ፣ኔዘርላንድ፣ፖርቱጋልን ጨምሮ የተገኙ ሲሆን ቅኝ ግዛትን ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የተሞከረ ና በዚሁ መሰረት በ 1914 በ ፈረንጆቹ አቆጣጠር አብዛኛው የ አፍሪካ ግዛት በ ቅኝ ገዢዎች የወደቀበት ሁኔታ ነበር።

Thursday, February 16, 2012

Keiseren Haile Selassie sammen med kong Haakon under statsbesøket i Oslo Nov.1954. (Emeror Haile Selassie with King Haakon of Norway during state visit Nov.1954) and Ethiopian Asylem seeker's paradox question.






I

Keiseren Haile Selassie  sammen med kong Haakon under statsbesøket i Oslo Nov.1954. (Emeror Haile Selassie  with King Haakon of Norway during state visit Nov.1954)



Keiseren Haile Selassie  sammen med kong Haakon under statsbesøket i Oslo Nov.1954. (Emeror Haile Selassie  with King Haakon of Norway during state visit Nov.1954)


Wednesday, February 8, 2012

''ቡና ጠጡ'' የኢትዮጵያውያን የመረጃ ምንጭ

''ቡና ጠጡ'' የኢትዮጵያውያን የመረጃ ምንጭ 
በ እኛ  ኢትዮጵያውያን ዘንድ ''ቡና ጠጡ'' የምትለው ጥሪ የማናውቅ የለንም።ቢያንስ ልጅ ሆነን ''ሂድ ማሙሽ አልያም ሚሚ እገን ቡና ጠጡ በል ወይም በይ'' ተብለን  ስንላክ አድገናል።እኛም  አድገን '' ካፈ'' ቤት ጎራ ብለን ቡና  እየቀመስን  የ ልባችንን ከ ወዳጅ ዘመድ  ጋር ያላወጋን  ማን ነን? ሰሞኑን አንድ ወዳጀ  ቡና እየጠጣ የተነሳውን  ፎቶ  አየሁ እና ብዙ ነገር ስለ ቡና ትዝ አለኝ። በመቀጠል  ግን ስለ ቡና ያነበብኩትን እና ያስተዋልኩትን ትንሽ ማለት ፈለግሁ።

ቡና  ለ እኛ ለ ኢትዮጵያውያን ከ ገጠር እስከ ከተማ   የሚጠጣ ትኩስ መጠጣችን ነው። ስለ ቡና አመጣጥ ስረ መሰረት የ እንግሊዝኛው ''አንሳይክሎፕድያ'' በ አንድ ሲኒ ቡና ስእል ስር እንዲህ የሚል ፅሁፍ በ ማብራርያነት ያስነብበናል :- 
''ቡና መልኩ ጥቁር አልያም ቡናማ ሲሆን የተገኘው ከ ኢትዮጵያ ነው '' ይላል ( http://en.wikipedia.org/wiki/Coffee)
አዎን ቡና አሁን ላለችው ዓለም የራሱ  ድርሻ  አንዳለው ብዙዎቻችን ልብ ያልነው አይመስልም:: ለ እንዱስትሪው አብዮት ዋነኛ የ አዳዲስ ሳይንሳዊ፣ፖለቲካዊ፣አና ምጣነሃብታዊ ሃሳቦች መፍለቅያነት ምክንያት ከነበሩት አንዱ  የ ኢንዱስትሪ አብዮት መጠንሰሻ የነበረችው  የ እንግሊዝ የቡና መጎንጫ ቤቶች ''ኮፊ ሃውስ '' ይባሉ የነበሩት ቤቶች ሚና ቀላል አንድልነበር ታሪክ ያስረዳናል:: 


Thursday, February 2, 2012

ምስጋናችን እና ወቀሳችን

የ ምስጋና ባህላችን ገና ብዙ ይቀረዋል።ወቀሳችንም እንዲሁ:: ለ አዚህ ማሳያ አዲስ አበባ ንግድ ሥራ ኮሌጅ ሳለሁ አንድ መምህራችን ክፍል ውስጥ ያሉን አይረሳኝም እውነተኛ ታሪክ ስለሆነ አስተማሪም ነው።መምህሩ ከ አንግሊዝ ሀገር የ ፒአችዲ ዲግሪአቸውን አንደያዙ እኛ ክፍል መመደባቸው ነበር::

Wednesday, February 1, 2012

'' እያከበሩ ማፍረስ'' ጠቅላይ ሚንስትሩ የተናገሩት

'' እያከበሩ ማፍረስ''  ጠቅላይ ሚንስትሩ  የተናገሩት

'' እያከበሩ ማፍረስ'' የምትለው አባባል  የ  ዛሬ ሶስት  ዓመት ገደማ ጠቅላይ ሚንስትሩ  የተናገሩት ትዝ ይለኛል።
ወቅቱ ዝናብ በመጠኑ የሚጥልበት ወቅት ነበር። ።እለቱ ቅዳሜ ነበር ከረፋዱ አራት ሰዓት አካባቢ ቦሌ መንገድ የሚገኘው የ ''ሚሊንየም'' አዳራሽ ውስጥጠቅላይ ሚንስትሩ የ ቀን አበል የተከፈላቸውንም ጭምር ይዘው  አልፎ አልፎ እንደሚአደርጉት የ ፓርትያቸውን ደጋፊ ወጣቶች ሰብስበው ንግግር እያረጉ ነው።የለበሱት ጃኬት እና ያረጉት የወጣት ኮፍያ ከ ወጣቶቹ ጋር አመሳስሏቸዋል።

The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church is in turmoil in Athens, Greece.

His Holiness Abune Mathias I, Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, met with Greece's Ambassador to Ethiopia, Antonios Sg...