ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, November 1, 2018

በቴፒ አዳዲስ የመከላከያ የደንብ ልብሶች በግለሰብ ቤት ተደብቆ ተገኝቷል። የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል በነዋሪዎች ላይ ግፍ እየፈፀመ ነው።ትምህርት ቤቶች እስካሁን አልተከፈቱም።የፌድራል ሰራዊት ካልገባ አዲስ ግጭት ሊያገረሽ ነው።

ጉዳያችን/Gudayacn Exclusive
ጥቅምት 23/2011 ዓም (ኖቬምበር 2/2018 ዓም)
(ከዜናው መጨረሻ የተለጠፈው የጃኖ ባንድ አዲስ ኢትዮጵያ የጥቁር አልማዝ የሚለው ሙዚቃ ቪድዮ ከዜናው ጋር ግንኙነት የለውም)
========================================
በደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ቡና አምራች ክፍል በቴፒ  ከተማ አዲስ ውጥረት አለ።ለጉዳያችን በተለይ በደረሰ መረጃ መሰረት ላለፉት 28 ዓመታት በህወሓት መራሹ የኢህአዴግ መንግስት ከተማዋን ማዕከል አድርጎ የተፈጠረው የእርስ በርስ የጎሳዎች የማቃቃር ሥራ እስከአሁን ድረስ ቴፒን አለቀቃትም።የህወሓት ኢህአዴግ ስርዓት ደጋፊዎች ሸክቾ ጎሳ አባላት በብቸኛነት በከተማዋ የስልጣን እርከን እንዲይዝ መደረጉ የሚታወቅነው።
ሌሎችብሔረሰቦች ኦሮሞ፣ከፋ፣ሸኮ፣መጀንግር።ዳውሮ።ወላይታ፣ጉራጌ፣ስልጤ፣ትግራይ፣ዓማራ፣ሲዳማ፣ሱማሌ፣ቤንች፣ሜኒት፣ዲዙ እና ሌሎች ነዋሪዎች በሙሉ ግን መብታቸው ተደፍጥጦ በተለያዩ ጊዚያት ግጭቶች እየተፈጠሩ የሰው ሕይወት ሲጠፋ ኖሯል።

ከአንድ ወር በፊት ወ/ሮ ሙፈርያ ከማል (የአሁኗ የሰላም ሚኒስትር ) ቴፒ ከተማ ተገኝተው እርቅ ለመፍጠር በጠሩት ስብሰባ ላይ አፍቃሪ ህወሓት - ኢህአዴግ ባለስልጣናት የሚፈልጉትን ሰው ብቻ መርጠው አዳራሽ እንዲገኝ አድርገው ህዝቡ ብሶቱን ለወ/ሮ ሙፈርያ እንዳያሰማ ስብሰባውን  እንደጠለፉት ተሰምቶ ነበር።ይህ ስብሰባ በኢትዮጵያ ቴሌቭዝንም ተዘግቦ ነበር።ጉዳዩን ተከትሎም የመከላከያ ኃይል ወደ ከተማዋ ገብቶ ከቆየ በኃላ  ወ/ሮ ሙፈርያ ከአዳራሽ ስብሰባውን ትተው እንደሄዱ የመከላከያ ኃይል ለቆ ሲወጣ የደቡብ ልዩ ኃይል ከተማዋን ተቆጣጠረ።


የደቡብ ልዩ ኃይል ግን ለቴፒ ከተማ አዲስ መከራ ይዞ መጣ።አፍቃሪ ኢህአዴግ የሸክቾ ተወላጆች የደቡብ ልዩ ኃይል ካላይ የተጠቀሱትን ውሁዳን እና ልዩ ልዩ ብሔረሰቦች ወጣቶች በግፍ እንዲደበደቡ በገንዘብ እና በጥቅማ ጥቅም እንደያዟቸው እና ሕዝቡን እየመረጠ ልዩ ኃይሉ እየደበደበ በመሆኑ  ከፍተኛ ቁጣ በከታማዋ ውስጥ ፈጥሯል።ህዝቡ አቤቱታውን ለማዕከላዊ መንግስት እንዲደርስለት ከፍተኛ ጥረት ቢያደርግም እስካሁን በደቡብ ክልል ባለስልጣናት መታፈኑ እና አሁን ጉዳዩ እጅግ አደገኛ ደረጃ ደርሶ የደቡብ ልዩ ኃይልን ጨምሮ በኃይል ሕዝብ ለማስወጣት ቀናት ሳይሆን ሰዓታት የቀሩት መሆኑን የሚመጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።


ይህ በእንዲህ እያለ አፍቃሪ ህወሓቱ የሸክቾ ተወካይ ነን የሚሉ ባለስልጣናት በግለሰብ መኖርያ ቤት ውስጥ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ ደብቀው ማስቀመጣቸው እና አንድ ሌሊት የደንብ ልብሱን ለብሰው የመከላከያ ሰራዊት ገባ ብለው የሌላውን ብሔር ተወላጆች ሊያጠቁ ዝግጅት ላይ እንደነበሩ በጥቆማ ይሰማል።ሕዝብ ቤቱ ይፈተሽ ብሎ አቤት ይላል።ሰሚ ያጣል።በመሀከል የመከላከያ ሰራዊት መጥቶ እንዲፈትሽ ሲደረግ በርካታ የመከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ ይገኛል። ይህ ሁኔታ በርካታ ጥያቄዎች አስነስቷል። የደንብ ልብሱ ከጦር ሰራዊቱ ውስጥ ካልተገኘ ከየት መጣ? በሌሎች አካባቢ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዘመን በክልሎች ውስጥ የሰራዊቱን ደንብ የለበሱ ነገር ግን የሰራዊቱ አባል ያልሆኑ ግለሰቦች መንግስት ለማስጠላት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አሉ ወይ? የሚሉት እና ሌሎች ጥያቄዎች አስነስቷል።

ለማጠቃለል በቴፒ በአሁኑ ሰዓት ከፍተኛ ውጥረት አለ።የጥቅምት ወር ሊጠናቀቅ ቀናት ቢቀሩትም ትምህርት ገና አልተጀመረም።የደቡብ ልዩ ኃይል ሰላም ለመፍጠር ሕዝቡን ሲያግባቡ የነበሩ ወጣቶች ጀርባቸው በሚዘገንን ደረጃ ተገርፈዋል፣ ግድያም ተፈፅሟል።በአሰቃቂ ደረጃ ጀርባቸው የተላጠ ወጣቶች ፎቶ ግራፍ ለጉዳያችን ደርሷል።ሕዝብ የደቡብ ልዩ ኃይል ይውጣልን መከላከያ ይግባ! ከተማዋ በራሷ ነዋሪዎች ትተዳደር የሚሉ ድምፆች አሁንም ሰሚ አላገኙም።አሁን ሕዝብ የመጨረሻ ጠርዝ ላይ ደርሷል።  በድንገት ተንስቶ ግፈኞቹ የደቡብ ልዩ ኃይል ሰራዊት ለመፋለም ሰዓታት  እየቆጠረ ነው።ይህ ደግሞ ከፍተኛ እልቂት ያስከትላል።ነዋሪው በሩን ዘግቶ ተቀምጧል።የደቡብ ልዩ ኃይል ቤቶች እየመረጠ በጭካኔ ነዋሪው ላይ ጥቃት እየፈፀመ ነው።ነዋሪው እራሱን ለመከላከል በህብረት ለመውጣት ዝግጅት ላይ ነው።የሰላም ሚኒስቴር አደጋ ከመድረሱ በፊት ይህንን እልቂት ሊከላከል ስለሚገባ ለጉዳዩ እጅግ አፋጣኝ እልባት መስጠት ይገባል።

የጥቁር አልማዝ ኢትዮጵያ እማማ የተሰኘው የጃኖ ባንድ አዲስ ሙዚቃ(ቪድዮ) 

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...