Friday, June 16, 2017

ሰበር ዜና - አዲስ አበባ የሚለውን ስም እና የጎዳናዎቿን ስም ለመቀየር በሕወሓት የሚታዘዘው የኢህአዴግ ምክር ቤት ዛሬ ስብሰባ ይቀመጣል



ሃያ አባላት እንደቀሩት የሚነገረው በሕወሓት የሚታዘዘው የኢህአዴግ ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 10፣2009 ዓም የአዲስ አበባን ስም ወደ ፊንፊኔ ለመቀየር፣የአዲስ አበባ ጎዳና ስሞችን በኦሮሞ ታሪክ ስሞች ለመቀየር፣የአዲስ አበባን የስራ ቋንቋ ኦሮምኛ ለማድረግ፣የኦሮምኛ ተናጋሪዎች አዲስ አበባ ላይ መሬት ካለ ሊዝ እንዲወስዱ ለመፍቀድ እና በአዲስ አበባ ውስጥ ያሉ ሁሉም መስሪያ ቤቶች ሥራ አስኪያጆች በኦሮሞ ተወላጆች ለመቀየር በሚሉ የውሳኔ ሃሳብ አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር ለማወቅ ተችሏል። ዜናውን ከአስተማማኝ ምንጭ መገኘቱን የኢሳት ራድዮ እና ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ በእየፊናቸው ሰኔ 9፣2009 ዓም ምሽት ገልጠዋል።

ሕወሓት አዲስ የመነታረኪያ አጀንዳ ለመሃል ሀገር ለመስጠት እና በዐማራ ክልል የተነሳበትን ብረት ያነሳ ሕዝባዊ ኃይል ለመዋጋት ያቀደ ይመስላል።አሁን በአዲስ አበባ ላይ ሊወሰድ ነው የተባለው እርምጃ ውሎ አድሮ እራሱ ሕወሓትን ጠልፎ እንደሚጥለው ለማወቅ ብዙ ውስብስብ ጉዳዮችን ማሰብ አያስፈልግም።

ከእዚህ በታች አለምነህ ዋሴ ጉዳዩን አስመልክቶ የለቀቀውን ዜና ያዳምጡ።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

''ሙዝ አትብላ! ጦጣዎች ከጫካ ሊመጡ ይችላሉ።'' ዓይነቱ የጀዋር ጊዜው ያለፈበት ትንተና በኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ላይ።

ቀይ ባሕር ዛሬ በዩቱብ አገኘን ብላችሁ በኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ላይ የምትሳለቁ የዘመናችን ባንዳዎች ግዴላችሁም ጊዜ እና ትውልድ ይፈርዳል! እናንተን ብቻ ሳይሆን ልጆቻችሁም ''አባታቸው በዩቱብ ኢትዮጵያ ...