እናታቸው እንግሊዛዊቷ ሲልቭያ ፓንክረስት ኢትዮጵያ በጣልያን ስትወረር በእንግሊዝ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በማቀጣጠል ተቃውመዋል።ንጉሡ በስደት በነበሩበት ወቅት አብረው ወጥተዋል ወርደዋል። በኃላም ከልጃቸው ሪቻርድ ፓንክረስት ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በኢትዮጵያ እስከ ሕይወታቸው ፍፃሜ ድረስ ኖረዋል።
ወ/ሮ ስልቭያ ፓንክረስት ዕረፍታቸውም ቀብራቸውም በኢትዮጵያ ነበር።የተቀበሩት በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው በመጪው ሰኞ የካቲት 13፣2009 ዓም ልጃቸው በሚቀበሩበት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን ነበር።
ወ/ሮ ስልቭያ ፓንክረስት ዕረፍታቸውም ቀብራቸውም በኢትዮጵያ ነበር።የተቀበሩት በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው በመጪው ሰኞ የካቲት 13፣2009 ዓም ልጃቸው በሚቀበሩበት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን ነበር።
የስልቭያ ፓንክረስት ልጅ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል እንዲመሰረት ያደረጉ ስለ ኢትዮጵያ ሲፅፉ እና ሲመራመሩ የኖሩ ምሁር ናቸው።ፕሮፌሰሩ ከ1940ዎቹ ጀምሮ እስከ ንጉሡ መውረድ ድረስ በኢትዮጵያ ከኖሩ በኃላ በ1970ዎቹ መጨረሻ እንደገና ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ምርምራቸውን ቀጥለዋል።ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስ በ90 አመታቸው ማረፋቸው እና በመጪው ሰኞ አዲስ አበባ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን የቀብራቸው ስነ ስርዓት እንደሚፈፀም ተነግሯል።
እረፍተ ነፍስ ለፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት መፅናናትን ለቤተሰቦቻቸው ይስጥልን።
የፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ልጅ ፕሮፌሰር አሉላ ፓንክረስ ግጥም ከእዚህ በታች ይመልከቱ።
ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com