በመጀመሪያው ክፍል ማለትም ከታህሳስ 21(Dec 30) - ጥር 14(Jan 24) እምቅ የኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻነት እና ድንቅ የሆነውን ባህላችን የምናስተዋውቅበት ጊዜ ሲሆን በእነዚህ ሶስት ሳምንታት የኢትዮጵያ ታሪካዊ ቦታዎች፣ መንፈሳዊ በዓላት፣ ወንዞች እና ሐይቆች፣ ተራሮች፣ የዱር እንሰሳት፣ ሙዚየሞች፣ ኪነ ጥበባችን፣ አለባበሳችን እና አመጋገባችንን ለዓለም በማሕበራዊ ሚድያዎች በሰፈው የምናስተዋውቅበት ይሆናል። በእነዚህ ሳምንታት ኢትዮጵያዊያን የባህል ልብሳቸውን እንደአመቺነቱ በሥራ ቦታቸው ለአንድ ቀን በመልበስ እና ፎቶአቸውን በማጋራት፣ ትናንሽ ስጦታዎችን ለሌው ማህብረሰብ በመሰጠት ኢትዮጵያን በቀላሉ የሚያስተዋውቁበት ነው። በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድም በሰፊው ይተዋወቃል። ኢትዮጵያ የጎብኚዎች አማርጭ እንድትሆነ በሰፈው ይሰራል።
በሁለተኛ ክፍል ከጥር 15 (25 Jan) - ጥር 22 (31 Jan) ድረስ ከኢትዮጵያ ውጪ በየሀገሩ ያሉ የንግድ ድርጅቶችን በየአካባባያቸው ባሉ ኢትዮጵያዊያን የሚተዋወቁበት ሳምንት ነው ።ይሄውም ኢትዮጵያዊን በዓለም አቀፍ ደረጃ በያሉበት ብቁ እና ተወዳዳሪ ድርጅቶች እንዲኖራቸው ያግዛል።
የኢትዮጵያዊያን ተወዳዳሪ መሆን ወደ ሀገር ቤትም ኢንቨስት ለማደረግ እና ከኢትዮጵያ ወደ ውጪ ለመላክ (Export) ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያዊያን በየአሉበት ሀገር የሚያውቃቸውን የኢትዮጵያውን የሒሳብ አማካሪዎች፣ ሱቆች፣ የሕግ ባለሞያዎች፤ ምግብ ቤቶች፣ የኢንፎርሚሸን ቴክኖሎጂ ተቋማት፣ ኮሌጆች፣ የመኪና መሸጫዎች፣ የሕክምና ተቅዋማት አድራሻ እና ስለአገልግሎታቸው በማኅበራዊ ሚድያ ይተዋወቃል።
ሶስተኛው ክፍል ከጥር 23 (Feb 1 ) - ይካቲት 7 (Feb 14) የኢትዮጵያ እንቨስትመንት ሳምንት ነው። በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያን እምቅ የእንቨስትመንት አቅም በኢንዱስትሪው፣ በእርሻ ፣ በኃይል አቅርቦት፣ በማዕድን ፍለጋ ዙርያ የሚተዋውቅበት ነው። በኤምባሲዎች በኩል ውይይቶችን፣ በኢንቨስትመንት ቢሮ በኩል ደግሞ የኢንቨስትመንት አማራጮችን የሚያሳዩ ዶክምነትሪዎች ለሌሎች እንዲጋሩ ይደረጋል። በኢትዮጵያም እስካሁን ኢንቨስት ያደርጉ በጎ ልምዳቸውን እንዲያጋሩ ይደረጋል። የታወቁ ኢትዮጵያዊያን የኢንቨስት አማራጮቻችንን እንዲያስተዋውቁ ይሆናል።
የመጨረሻው እና አራተኛው ክፍል ከየካቲት 8 (Feb 15) - የካቲት 14 (Feb 21) የመስጠት ሳምንት (Giving weeks) ነው - በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያውያን በእያሉበት በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ መልካም ፕሮጀክቶች ማለትም ሕዳሴ ግድብ፣ ኮቪድን ለመከላከል፣ ለበጎ አድራጊ ድርጅቶች እና ለሌላም ፕሮጀችክቶች የገንዘብ ደጋፍ የሚያደርጉበት እና ለኢትዮጵያ የሚጠቅሙ መልካም ግንኙነቶችን የሚፈጥሩበት ሳምንት እንደሚሆን ዶ/ር በላቸው አብራርተዋል።



