Pages

Pages

Saturday, June 7, 2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሰሞኑ ቃለ መጠይቅ ( አራቱም ክፍል ቃለ መጠይቅ ቪድዮ እዚህ ያገኛሉ)

የኢትዮጵያ የ20ኛውና የ21ኛው ክ/ዘመን ትውልድ ሲታገልለት የነበረው አንዱና ቀዳሚው ጉዳይ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ልማት ጉዳይ ነው። ጠ/ሚ/ር ዐቢይ በእዚህ ሳምንት ለኢቢሲ የሰጡት ባለ አራት ክፍል ቃለ መጠይቅ ማድመጥ እና የኢትዮጵያን ርዕይ መጋራት የሁሉም ባለ በጎ ሕሊና ዜጋ ግዴታ ነው። ድንቅ ማብራርያ፣ርዕይ እና የሥራ ውጤት ሁሉ በቃለ መጠይቁ በሚገባ ተብራርቷል።

ክፍል 1


ክፍል 2


ክፍል 3



ክፍል 4





===================////===============


Saturday, May 31, 2025

አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ የኢትዮጵያን የቀይ ባሕር ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ዓለም አቀፋዊ የቀይ ባሕርን በሙሉ መብትነት የመጠቀም ጥያቄ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን የአንድ ክልል ጥያቄ አድርገው ለማቅረብ የሞከሩበት መንገድ በራሳቸው ላይ የመተኮስ አደገኛ አካሄድ ነው።


=========
ጉዳያችን ምጥን
=========
አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ በአፍሪካ ውስጥ በ1980ዎቹ እና 90ዎቹ ከተነሱት የዓለማችን አምባገነኖች የሚመደቡ ብቻ ሳይሆኑ በእነኝህ ዓመታት የተነሱ አምባገነኖች የቀዝቃዛው ጦርነት ውጤቶች ስለሆኑ የተካኑበት ጉዳይ አንድ እና አንድ ነው።ይሄውም በ20ኛው ክ/ዘመን ያረጀው እና ያፈጀው ግጭት፣ሴራ፣እና ጦርነትን ብቻ አራግቦ ስልጣን ማቆየት ነው። አቶ ኢሳያስ የሊብያውን ሙሐመድ ጋዳፊ ከሚያደንቁ መሪ አንዱ ነበሩ። ጋዳፊ ከስልጣን ሲወገዱ ቀኝ እጃቸው የተቆረጠ ያህል በሃዘን መጎዳታቸውን የሚያውቋቸው ይናገራሉ።

አቶ ኢሳያስ የ20ኛውን ክ/ዘመን የሴራ ፖለቲካ በ21ኛው ክ/ዘመን የዲጂታል እና የአርቴፍሻል ኢንተለጀንስ ዘመን ላይ ዓለም የፖለቲካውን፣የምጣኔ ሃብቱንም ሆነ የወታደራዊውን ዓለም በምን ያህል ፍጥነት እንደቀየረው እና ዓለም የሚሰራበት አሰራር እንዳልገባቸው ብቻ ሳይሆን በጣም እንደከበዳቸው ለማወቅ ብዙ ሊቅ መሆን አይፈልግም።

በአቶ ኢሳያስ እና በኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መሃከል ያለው የዕውቀት፣ነገሮችን በፍጥነት የመረዳት እና የመጪውን ዘመን በሚገባ የመተንበይ አቅም የሰማይና የምድር ያህል ብቻ እርቀት ያለው አይደለም። ዶ/ር ዐቢይ የብዙ ክህሎቶች ባለቤት መሆናቸው ብቻ አይደለም፣አንባቢነታቸው እና ነገሮችን በፍጥነት የመረዳት እና ችግርን ወደ መልካም የመቀየር ክህሎትም ብቻ አይደለም። ዶ/ር ዐቢይ ብቁ አማካሪዎች ከማቅረብ እና ከእነርሱም የመማር ክህሎታቸው ሁል ጊዜ እጥፍ እርምጃ እንዲቀድሙ ያደርጋቸዋል።

የአፍሪካ መሪዎች አንዱ ችግር ብቁ አማካሪ አለማቅረብ እና አዋቂ አለመስማት ነው። ዶ/ር ዐቢይ በእዚህ በኩል ችግር የለባቸውም።ከአርበኞች ግንቦት 7 ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋን፣ከአብን የአይቲ ባለሙያ፣ከቀድሞ የኦነግ ሰዎች በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ሌላው ቀርቶ ህወሐትን ሲያገለግሉ የነበሩትን የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ አማካሪ አድርገው የኢትዮጵያን ሥራ ለመስራት ዶ/ር ዐቢይ ልቀታቸውን አሳይተዋል። አቶ ኢሳያስ ዶ/ር ዐቢይ ያሉበት የልቀት ደረጃ ለመድረስ ከአሁን በኋላ ሌላ የ34 ዓመታት ቢጨመርላቸውም ሊደርሱበት ፈጽሞ አይችሉም። ይህ ተራ ትንበያ አይደለም። ይልቁንም አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ አንድ ሺህ ኪሎ ሜትር የባሕር በር ከሦስት አስር ዓመታት በላይ ይዘው ለኤርትራ ሕዝብ ብልፅግና ሳይሆን አንድ የረባ ህንጻ አስመራ ላይ አልቀየሩም። በንጉሱና በወታደራዊ ዘመን የተሰሩና የታደሱ ስታድዮም ላይ ዘንድሮም የኤርትራ 34ኛ ዓመት በዓል ብሎ የማክበር ያህል የሚያሳፍር ጉዳይ ምን አለ?

አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ በዘመናቸው ሁለት ትውልድ ከኤርትራ ተሰዶ በደርዘን የሜዴትራንያን ባሕር የዓሳ ነባሪ ''ሲሳይ '' ሲሆን እና በሊብያ በረሃዎች ሲንከራተት ማየት እንዴት ህሊና ይሰብራል?

ከ34 ዓመታት በኋላም አቶ ኢሳያስ በዘንድሮ ''የነፃነት በዓል '' ብለው ቀድሞ በኢትዮጵያ የተገነባው ስታድዮም ውስጥ ባደረጉት ንግግር አዲስ የኢትዮጵያን ህዝብ በጎሳ ለማጋጨት ያለመ ንግግር አድርገዋል።|

አቶ ኢሳያስ በእዚሁ በግንቦት 16፣2017 ዓም ባደረጉት ንግግር ላይ የኢትዮጵያን የቀይ ባሕር ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ዓለም አቀፋዊ የቀይ ባሕርን በሙሉ መብትነት የመጠቀም ጥያቄ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን የአንድ ክልል ጥያቄ አድርገው ለማቅረብ የሞከሩበት መንገድ በራስ ላይ የመተኮስ አደገኛ አካሄድ አሳይተዋል።ይህ ንግግራቸው የተስፋ መቁረጥ ንግግር መሆኑን አስረግጦ መንገር ግን ስህተት አይሆንም። ሰው ተስፋ ሲቆርጥ የሚያደርገው የማይቧጠጥ ነገር ይቧጥጣል።

አቶ ኢሳያስ በእዚሁ ንግግራቸው ላይ እንዲህ ማለታቸው ተስምቷል፡ ፟

"ሊያቀርቡ የሚፈልጓቸው ምክንያቶች ብዙ ናቸው። የውሃ ጉዳይ፣ አባይ እና ቀይ ባሕር፣ የባሕር በር ማግኘት፣ የኦሮሞ ሕዝብን የማይወክል የኦሮሙማ አስተሳሰብ፣ የኩሽ እና የሴም ግጭት፣ የአፋር ሕዝብ እና መሬትን ለዚህ አጀንዳ መጠቀም እንዲሁም ጦርነት በሰፊው መቀስቀስ

በእዚህ ንግግራቸው አቶ ኢሳያስ የኢትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን ስለ ዓባይ ግድብ እና የቀይባሕር ጉዳይ የሚያነሳው አንድ ክልል ነው የሚል ፌዝ አዘል ንግግር ነው። ስለ ኩሽና የሴም ጉዳይ ሲያነሱም የተስፋ መቁረጥ ልኩ የመጨረሻ የጎሳ ካርድ በኢትዮጵያ ላይ ለመምዘዝ የመውተርተር ጉዳይ ነው። አቶ ኢሳያስ ግን ይህ መንገድ እንደማያዋጣቸው በትክክል ያውቁታል። በብዙ ዕውቀት ቢጎዱ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጠንቅቆ በማወቅ ግን ጉድለት ያለባቸው አይመስልም። የኢትዮጵያ ህዝብ በዓባይ እና በቀይባሕር ጉዳይ እንደማይደራደር ብቻ ሳይሆን ማንም መንግስት ጋር በእነኝህ ቁልፍ የህልውናው ጉዳይ ላይ አብሮ ይቆማል። እንዴት በቅጽበት አንድነቱን እንደሚፈጥር እና እንደግስላ ተቆጥቶ እንደሚቆም በሚገባ ያውቁታል። 

ለማጠቃለል አቶ ኢሳያስ የቀይባሕር ጉዳይ የአንድ ክልል ጥያቄ እንዳልሆነ እርስዎም ጠንቅቀው ያውቁታል።የኢትዮጵያ ህዝብ ሲወድ ይንከባከባል፣ ከዚያም አልፎ ''ኢሱ! ኢሱ!'' ይላል።ሁሉን እረስቶ ማለት ነው። ሊከፋፍሉት ሲሞክሩ ግን ቢያንስ በምፅዋ በቀይባሕር ውስጥ ለኢትዮጵያ (ኤርትራን ጨምሮ) የተሰዉትን ልጆቹን ያስታውሳል።ይቆጣል። አሁን አቶ ኢሳያስ የኢትዮጵያን ሕዝብ አስቆጥተዋል። በዘር ለመከፋፈል የተጠቀሙበት ንግግር አቶ ኢሳያስ ኢትዮጵያን በዘር የመከፋፈል ሴራ ውስጥ የለሁበትም በማለት ከእዚህ በፊት እየማሉ የተናገሩትን ሁሉ ሃሰት መሆኑን ያረጋገጠ ነው። ''የአፍ ወለምታ በቅቤ አይታሽም '' እንዲሉ።ባጭሩ አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያሰሙት ከፋፋይ እና ጎሰኛ ንግግር መልሶ ወደራሳቸው ላይ እንደሚባርቅ እረስተውታል።
====================////=============

Wednesday, January 15, 2025

የግሪክ አቴንሱ ''ኢትዮጵያዊው'' አውርቶ አዳሪው ''ዲያቆን'' እና ከጥንትም የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው የ''አውርቶ አደር'' ማንነት



=============
የጉዳያችን ማስታወሻ
=============

ከጥንትም የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው ''አውርቶ አደር'' ማንነት 

የኢትዮጵያ የታሪክ ስብራት ዋነኛዎቹ ምክንያቶች አውርቶ አደሮች ናቸው።ይህ አደር የሚለው የአማርኛችን ቃል ከፊት አንድ ቃል እያስከተለ ''አደር'' የሚለውን ቃል ብዙ ፍቺ ያሰጠዋል። ወቶአደር(ወታደር)፣ላብአደር፣ ሰርቶአደር፣ወዝአደር የሚሉትን ቃላት እናውቃቸዋለን። በስማቸው ያልጠራናቸው እና መጥራትም የሚገባን ''አውርቶአደር'' የሚባሉትን ነው።

ኢትዮጵያን ወደፊት ለማስፈንጠር የተጉቱ የቀደሙ የኢትዮጵያ ነገስታት፣ምሑራን፣ሃሳብ አመንጪ ዜጎችን ሁሉ አላሰራ ያለ አፉን በነጠላ ሸፍኖ አንዳች ፍሬ ነገር ሳይሰራ እያልጎመጎመ ሲያወራ ውሎ የሚያድረው አውርቶ አደር ነው። አፄ ቴዎድሮስ ከዘመናቸው ቀድመው የሚያስቡ መሪ ነበሩ።ሌላው ቀርቶ መጪው የሀገር መከላከያ በዘመናዊ መሳርያ ካልታገዘ ሃገር መጠበቅ አዳጋች መሆኑን ስላወቁ መድፍ እንዲሰራላቸው ትዕዛዝ ሲሰጡ፣አውርቶ አደር ያወራ ነበር።

ዳግማዊ ምንሊክ አውርቶ አደር ሳይሆኑ ሰርቶ አደር ነበሩ።ከዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ እስከ የትራንስፖርት ስራ፣ከአካባቢ ጥበቃ እስከ ዘመናዊ ጦር ማደራጀት፣ከስልክ እና መኪና ማስመጣት እስከ አብያተክርስቲያናት ግንባታ ሰርቶ አደር ነበሩ። አውርቶ አደሩ ግን በዘመናቸው ሰላም የነሳቸው ጊዜ በቀላሉ የሚቆጠር አልነበረም። በእያንዳንዱ ስራቸው አውርቶ አደር እየገባ ለሀገራቸው የሚሰሩትን ለማደናቀፍ ሲያወራ ውሎ ሲያወራ ያድር ነበር። ዳግማዊ ምንሊክ መኪና አስመጥተው የመጀመርያው ነጂ ሲሆኑ፣ሊገዝቱ የቃጡ ነበሩ። ሲኒማ ቤት ከፍተው ለሕዝብ ሲያሳዩ አውርቶ አደር ''የሰይጣን ቤት'' ብሎ ሲያወራ ዋለ። መጪው የታያቸው ዳግማዊ ምንሊክና እቴጌ ጣይቱ የመጀመርያውን ዘመናዊ ሆቴል ጣይቱ ከፍተው ንጉሱና ንግስቲቱ እየገቡ ሰውን ለማለማመድ ሲሞክሩ አውርቶ አደሩ ሴት እንዴት ሆቴል ገብታ ትበላለች? እያለ ይሳለቅ ነበር። አውርቶ አደር በየዘመኑ ነበር። በዘመናችንም ጨምሮ።

አሁን ባለንበት ዘመን አውርቶ አደር እንደቀድሞው አፉን በኩታ ሸፍኖ የሚንሾካሾክ ወይንም ጠላና ጠጅ ቀኑን ሙሉ እየጠጣ ሲያወራ የሚውል አይደለም። የማኅበራዊ ሚድያ ላይ ተጥዶ ለኢትዮጵያም ለወገኑም አንድ ሳይሰራለት ብቻ ሳይሆን የሚሰሩትን ሲያብጠለጥል ሲሳለቅ የሚውል  በአውርቶ አደርነቱ ደግሞ ዩቱብና ሌሎች የማኅበራዊ ሚድያ ተቋማት ገንዘብ ስጡኝ እያለ ሲማጸን የሚኖር ነው።

የዘመናችን አውርቶ አደር ከተማ ጸዳ፣መብራት ተተከለ ሲባል ሰርቶ አደሩ በሰራው የሚነቅፍበትን ሲያስብ ያድራል። የአድዋ ሙዜም ሊሰራ ነው ሲባል፣ የምንሊክን ሃውልትን ሊነቅሉት ነው ይላል፣ ይሄው አውርቶ አደር።ሃውልቱም ደምቆ ያልነበረ ሙዜም ተሰርቶ ሲያልቅ ደግሞ ሙዜም ከሚሰራ ይልና ሌላ ትረካ ይጀምራል።አውርቶ አደር ስራው አውርቶ ማደር ብቻ ስለሆነ ማመስገን ብሎ ነገር አያውቅም። ሌላው ቀርቶ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያልታደሰው የብሔራዊ ቤተመንግስ ሲታደስ፣ሸረሪት ያደራባቸው የሀገር ቅርሶች በወጉ ሲቀመጡ፣የሳይንስ ሙዜም ሲሰራ፣ግዙፍ ብሔራዊ መጻሕፍት ቤት ተሰርቶ ሲያልቅ፣የብሔራዊ መዛግብት መረጃ ማዕከል ሲሰራ፣የስቶክ ኤክስቸንጅ ማዕከል ስራ ሲጀምር፣የጎንደር አብያተ መንግስታት ታድሰው ከተማው ሲደምቅ ሳይቀር አውርቶ አደር አይኑን እያሸ ይመጣል። ያው እንደለመደው ለማውራት።

የዘመናችን አውርቶ አደሮች ምሳሌ እንጥቀስ ብንል እጅግ ብዙ ናቸው።ከአክቲቪስት ጀዋርን ብንወስድ አንዲት ጉድጓድ ውሃ ላላስቆፈረለት እና አንዲት ብርጭቆ ውሃ እንዲጠጣ ያላደረገውን የኦሮሞ ወንድሞቻችንን በአውርቶ አደርነት ነግዶ ጨርሶ አሁን በኢትዮጵያ ስም አውርቶ ለማደር እየሞከረ ነው። አውርቶ አደሮች እንዲህ ናቸው። ከአንዱ ጎራ ወደ ሌላ ለመዝለል ችግር የለባቸውም።በዩቱብ በአማራ ክልል ህዝብ የሚነግዱት አውርቶ አደሮች ለህዝቡ አንድ ቀን አንዲት ሳንቲም ልከው የአንድ ትምህርት ቤት መገልገያ የሚሆን አንዲት ቾክ አልላኩለትም። በስሙ አውርተው እያደሩ ግን በዩቱብ የልጆቻቸውን የትምሕርት ቤት ወጪ ይሸፍናሉ። የኢትዮጵያ ጉዳይ በሰርቶ አደሮች እና በአውርቶ አደሮች መሃል የሚደረግ ፍልምያ ነው። ህዝብ አውርቶ አደሮችን እየለየ ብቻ ሳይሆን እያራገፈ እና በስሜ አትነግዱ፣ከጫንቃዬ ውረዱ እያለ ነው።የኢትዮጵያ ሀገራዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ችግር ፈጣሪዎች አውርቶ አዳሪዎች ናቸው።በእዚህ ዘመን ''አውርቶ አደሮች'' እና ''ሰርቶ አደሮች'' ተለይተዋል።


=================////============