Tuesday, February 19, 2019

የካቲት 12 ሰላሳ ሺህ ኢትዮጵያውያን የሞቱበት የሰማዕታት ቀን የተወካዮች ምክር ቤት በብሔራዊ ደረጃ እንዲከበር እንዲወስን ይፈርሙ።

የተወካዮች ምክር ቤት እንዲወስን ፊርማዎን እንዲያሳርፉ በሰማዕታቱ ስም ይለመናሉ።
የካቲት 12 /1929 ዓም አዲስ አበባ ከሰላሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎችዋ በ አንዲት ጀንበር ሰማዕትነት የተቀበሉባት ቀን ነበረች።በዓሉ ላለፉት አርባ ዓመታት በተለየ ደግሞ ላለፉት ሀያ ስምንት ዓመታት አከባበሩ ደብዝዟል።አከባበሩ መደብዘዙ አደጋ መሆኑን የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የካቲት 12/2011 ዓም ባቀረበው የምሽት ዜና እወጃ ላይ የታሪክ ባለሙያዎችንም አነጋግሮ አረጋግጧል።
በዓለማችን ላይ አይደለም ለሰላሳ ሺህ ሰማዕት ለአንድ ሰማዕትም ብሔራዊ በዓል ተደርጎ ታስቦ ይውላል።በኢትዮጵያም እስከ 1968 ዓም ድረስ የየካቲት 12 የሰማዕታት ቀን ትምህርት ቤቶች ተዘግተው በመንግስት መስርያቤት ሳይቀር በከፍተኛ ደረጃ ተከብሮ ይውል ነበር።በ1968 ዓም በዓሉ አከባበሩ ዝቅ ብሎ ታስቦ ብቻ እንዲውል ያደረገው የደርግ መንግስት ነው።ከደርግ ዘመን በኃላ ላለፉት 28 ዓመታት በባሰ መልኩ በዓሉ የመገናኛ ብዙኃንን ሽፋን ሳይቀር በበቂ መልኩ ሳያገኝ ቀርቷል። ይህ በእራሱ ብሔራዊ አደጋ ነው።
ስለሆነም የኢትዮጵያ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የካቲት 12 ብሔራዊ የሰማዕታቱ የመታሰቢያ ቀን ሆኖ በብሔራዊ ደረጃ በመላዋ ኢትዮጵያ በአዋጅ እንዲከበር እንዲያደርግ ይህንን ፊርማ ማሰባሰብ አስፈላጊ ሆኗል።
የበዓሉ በብሔራዊ ደረጃ የመከበሩ ፋይዳ የአዲስ አበባ ከተማ እጅግ አሰቃቂ ውጣ ውረድ አልፋ እዚህ መድረሷን ብቻ የሚያሳይ ሳይሆን ኢትዮጵያውያን ዘር፣ቋንቋ እና ኃይማኖት ሳይለያያቸው በደም በተለወሰ መስዋዕትነት የገነቧት ሀገር መሆኗን ለትውልዱ የማስተማርያ አይነተኛ መንገድ ነው።
ስለሆነም ይህንን ፊርማ በመፈረም እና ላልሰሙም በማካፈል ኃላፊነትዎን ይወጡ!
የካቲት 12 ሰላሳ ሺህ ኢትዮጵያውያን የሞቱበት የሰማዕታት ቀን በብሔራዊ ደረጃ እንዲከበር የተወካዮች ምክር ቤት እንዲወስን ፊርማዎን እንዲያሳርፉ በሰማዕታቱ ስም ይለመናሉ።
ለመፈረም ይህንን ማስፈንጠርያ (ሊንክ) ይጫኑ http://chng.it/ZNT87PstCq 
ጉዳያችን / Gudayachn 


No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...