ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, September 5, 2018

የህዳሴው ግድብ ሲገለጥ- ልዩ የምርመራ ዘገባ ፊልም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊመለከተው የሚገባ ፊልም።

- የግድቡ ፕሮጀክት ከሜቴክ (የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን) ጋር የ25 ቢልዮን ብር ስራ ውል ገብቷል፣
- እስካሁን 16 ቢልዮን ብር  ለሜቴክ ተከፍሏል፣ ያልሰሩ ማኅበራት ሁሉ እንደሰሩ እየተደረገ ክፍያ ሲፈፀም ነበር።
- ሜቴክ እየተማርን ልንሰራ ነው ተለማመድንበት እያለ ነው።
- አንድም የግድብ ግንባታ ልምድ የሌለው ሜቴክ ከሰባት ዓመት ብክነት በኃላ አለመቻሉ ተረጋግጦ ኮንትራቱ ልምድ ላላቸው መስጠት ተጀምሯል፣
- ሳሊን በሜቴክ በኩል ያለው ሥራ ለትክክለኛ ሰው መስጠቱ ተገቢ ነው  ይላል።ሳሊኒ የተሰጠውን 75% ሰርቷል ይላል ዘገባው፣
- እስካሁን ይጠናቀቃል የተባለው ግድብ ስራ እስካሁን በ7 ዓመታት ውስጥም ገና ከ25 እስከ 30% ነው የሔደው።
- ግድቡ ከስድስት ዓመታት  በፊት ነው ኦዲት የተደረገው።በዚያን ጊዜም በሶስት ዓመታት ውስጥ የቀረቡት ሪፖርቶች እርስ በርስ የተጣረሱ ነበሩ ፣
- እስካሁን ግን ሌላ ኦዲት አልተደረገም።
-  የሜቴክ ኃላፊ አቶ አብዱላዚዝ 'በተጨባጭ ሲታይ ያደረስነው ጉዳት ነው ያመዘነው። ስራውን ያለጨረታ ነው የወሰድነው '' ብለዋል፣
-  በግድቡ ሥራ ላይ ከፍተኛ የፕሮጀክት መዝረክረክ ብቻ ሳይሆን ብክነት ታይቷል፣
- የደን ምንጣሮን 30% የማይሞላ ተሰርቶ ክፍያው ግን 50% ለሜቴክ ተከፍሏል፣
- አዲሱ የሜቴክ አስተዳደር ስራውን ለመቀጠል የተረከብነው የመረጃ ክፍተቶች ችግር አለ የኤሌክትሮ መካኒካል ስራን ለውጭ ኩባንያ እየተሰራ እየተሰጠ ነው፣
-  ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አህመድ ''የፕሮጀክት ችግሮቹ ተወግደው ስራውን መቀጠል አለብን።ስራው ትልቅ ትልም ነው።ካልሰራነው እንደ ሀገር የሚያሳፍር።ከሰራነው እጅግ የሚያኮራ ነው''  ብለዋል።

የምርመራ ዘገባ አዘጋጅ = ዋልታ ኢንፎርሜሽን 
ቪድዮ ከዋልታ ኢንፎርሜሽን ዩቱብ 
ቀን ነሐሴ 29/2010 ዓም 


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

No comments:

ወቅታዊ የዓለም ሁኔታ እንድንነታረክ ዕድል የሚሰጥ አይደለም።ብንነቃ መልካም ነው።

========== ጉዳያችን ወቅታዊ ========== የዓለም ታሪክ እንደሚያስተምረን ዓለም በወሳኝ የእጥፋት(turning point) ታሪኮች ውስጥ አልፋለች። እነኝህ የእጥፋት ጊዜዎች የዋዛና የፈዛዛ ጊዜ አይደሉም።መላው ዓለ...