ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, September 5, 2018

የህዳሴው ግድብ ሲገለጥ- ልዩ የምርመራ ዘገባ ፊልም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊመለከተው የሚገባ ፊልም።

- የግድቡ ፕሮጀክት ከሜቴክ (የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን) ጋር የ25 ቢልዮን ብር ስራ ውል ገብቷል፣
- እስካሁን 16 ቢልዮን ብር  ለሜቴክ ተከፍሏል፣ ያልሰሩ ማኅበራት ሁሉ እንደሰሩ እየተደረገ ክፍያ ሲፈፀም ነበር።
- ሜቴክ እየተማርን ልንሰራ ነው ተለማመድንበት እያለ ነው።
- አንድም የግድብ ግንባታ ልምድ የሌለው ሜቴክ ከሰባት ዓመት ብክነት በኃላ አለመቻሉ ተረጋግጦ ኮንትራቱ ልምድ ላላቸው መስጠት ተጀምሯል፣
- ሳሊን በሜቴክ በኩል ያለው ሥራ ለትክክለኛ ሰው መስጠቱ ተገቢ ነው  ይላል።ሳሊኒ የተሰጠውን 75% ሰርቷል ይላል ዘገባው፣
- እስካሁን ይጠናቀቃል የተባለው ግድብ ስራ እስካሁን በ7 ዓመታት ውስጥም ገና ከ25 እስከ 30% ነው የሔደው።
- ግድቡ ከስድስት ዓመታት  በፊት ነው ኦዲት የተደረገው።በዚያን ጊዜም በሶስት ዓመታት ውስጥ የቀረቡት ሪፖርቶች እርስ በርስ የተጣረሱ ነበሩ ፣
- እስካሁን ግን ሌላ ኦዲት አልተደረገም።
-  የሜቴክ ኃላፊ አቶ አብዱላዚዝ 'በተጨባጭ ሲታይ ያደረስነው ጉዳት ነው ያመዘነው። ስራውን ያለጨረታ ነው የወሰድነው '' ብለዋል፣
-  በግድቡ ሥራ ላይ ከፍተኛ የፕሮጀክት መዝረክረክ ብቻ ሳይሆን ብክነት ታይቷል፣
- የደን ምንጣሮን 30% የማይሞላ ተሰርቶ ክፍያው ግን 50% ለሜቴክ ተከፍሏል፣
- አዲሱ የሜቴክ አስተዳደር ስራውን ለመቀጠል የተረከብነው የመረጃ ክፍተቶች ችግር አለ የኤሌክትሮ መካኒካል ስራን ለውጭ ኩባንያ እየተሰራ እየተሰጠ ነው፣
-  ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አህመድ ''የፕሮጀክት ችግሮቹ ተወግደው ስራውን መቀጠል አለብን።ስራው ትልቅ ትልም ነው።ካልሰራነው እንደ ሀገር የሚያሳፍር።ከሰራነው እጅግ የሚያኮራ ነው''  ብለዋል።

የምርመራ ዘገባ አዘጋጅ = ዋልታ ኢንፎርሜሽን 
ቪድዮ ከዋልታ ኢንፎርሜሽን ዩቱብ 
ቀን ነሐሴ 29/2010 ዓም 


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...