ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, August 27, 2015

ጥንታዊቷ እና የዓለም ቅርስ የሆነችው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በማየሽቷ ኦስሎ ትታያለች Ancient and world heritage Ethiopian church is now visible in Majorstuen church, Oslo. እናመሰግናለን ኖርዌይ!! Thank you Norway!! Tusen Takk Norge !!

 ማየሽቷ ቤተ ክርስቲያን (Majorstuen kirks)፣ Majorstuen Church 
 ማየሽቷ ቤተ ክርስቲያን (Majorstuen kirke)፣ Majorstuen Church

እናመሰግናለን ኖርዌይ!!

ጥንታዊቷ እና የዓለም ቅርስ የሆነችው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በማየሽቷ ኦስሎ ትታያለች።

ከመጪው ቅዳሜ ነሐሴ 23/2007 ዓም (ኦገስት 29/2015) ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል፣አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ቀድሞ ከነበረችበት ''ጋምለ ኦስሎ'' ወደ ''ማየሽቷ ካቴድራል'' ትገባለች።የቤተ ክርስቲያኗ የህንፃ ኮሚቴ ቤተ ክርስቲያኗ የእራሷ መሬት በግዥ እንዲኖራት እና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን የህንፃ ዲዛይን የያዘ ቤተ ክርስቲያን ለመስራት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ሲሆን እስካሁን በአጭር ጊዜ ውስጥ በእግዚአብሔር እርዳታ አስደናቂ እርምጃዎችን እየሄደ ለመሆኑ ብዙዎች ምስክር ናቸው። ኮሚቴው ላለፉት አምስት አመታት ቤተ ክርስቲያኗ ስትገለገልበት የነበረው ''ጋምለ ኦስሎ የሚገኘው ቤተ ክርስቲያን በመጥበቡ በኦስሎ ከተማ ከሚገኙት ካቴድራል ውስጥ አንዱ የሆነው ''የማየሽቷ ካተድራልን'' ቤተ ክርስቲያን እንድትጠቀም የኖርዌይ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ኃላፊዎችን  ከአቡነ ኤልያስ ጋር ሆኖ በማነጋገር ካቴድራሉን እንድንጠቀም የኖርዌይ ከፍተኛ የቤተ ክርስቲያኒቱ ኃላፊዎች ከወራት በፊት መወሰናቸው ይታወቃል። በእዚሁም መሰረት ከመጪው ቅዳሜ ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት በእዚሁ በማየሽቷ ካቴድራል ይሆናል።የቤተ ክርስቲያኑ አድራሻ  Kirkeveien 84, oslo; Majorstua,Oslo.  ''ኖርዌይ እናመሰግናለን!! ለኖርዌይ ሕዝብ እና ሰላም እንፀልያለን'' አንድ የቤተ ክርስቲያኑ አገልጋይ ዜናውን ስሰማ የተናገረው።አዎን! በዘመናችን ከሀገር ወጥተን በተገኘንበት ሀገር ሁሉ በጎ ያደረጉልንን ልናመሰግን ውለታቸውንም ልናስብ ይገባል።

Thank you Norway!!

Ancient and world heritage Ethiopian church is now visible in Majorstuen church, Oslo.


Ethiopian Orthodox Tewahedo St.Gebriel-Abune Teklehaimanot Church started its spiritual service in Majorstuen church,Oslo. It was known the church was providing full weekly service at Gamle Oslo for the past 5 years.The Norwegian church top leaders have negotiated with Ethiopian Orthodox Tewahedo church bishop Abune Elias some months back and allowed the church to provide its service in Majorstuen church starting from the coming Saturday,August 29/2015.

''Thank you Norway!! I pray for Norway and beloved people too to be save for long time and ever!!'' one Ethiopian Orthodox church service man explained his happiness, when he has heard as the church will shift from Gamle Oslo to Majorstuen church.

Tusen Takk Norge !!

 Ancient og verdensarv Etiopiske kirke er nå synlig i Majorstuen kirke, Oslo.

Etiopiske ortodokse Tewahedo St.Gebriel-Abune Teklehaimanot kirke startet sin åndelige tjeneste i Majorstuen kirke, Oslo. Det var kjent at kirken var å gi full ukentlig service på Gamle Oslo de siste 5 år.The norske kirketoppledere har forhandlet med den etiopisk-ortodokse kirke biskop Abune Elias noen måneder tilbake, og tillot kirken for å tilby sine tjenester i Majorstuen kirke fra den kommende lørdag august 29/2015.

'' Takk Norge !! Jeg ber for Norge og elskede folk for å være redde for lang tid og noen gang !! '' en Etiopisk-Ortodokse kirks service mann forklarte sin lykke, når han har hørt som kirken vil skifte fra Gamle Oslo til Majorstuen kirke.

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ነሐሴ 21/2007 ዓም (ኦገስት 27/2015)

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።