Thursday, May 9, 2013

የሕገ መንግስቱ አንቀፅ 30 ይከበር! የዲሞክራሲ መብታችን ወደፊት እንጂ ወደኃላ መንሸራተት አይገባውም-ሚያዝያ 30፣1997 ዓም የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ (ቪድዮ)

ሚያዚያ 30፣1997ዓም ዕሁድ አዲስ አበባ ምናልባትም በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የ ዲሞክራስያዊ ለውጥ የሚጠይቅ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጎ ነበር። በሚልዮን የሚቆጠር ሕዝብ በሰላም ወጥቶ በሰላም የገባበት- ሁሉም ነገር ካለ አንዳች እረብሻ የተጠናቀቀበት ታሪካዊ ሰልፍ ነበር።ይህ ሰልፍ ከተደረገ እነሆ ስምንት አመታትን አሳለፈ።
  • የዲሞክራሲ መብታችን ወደፊት እንጂ ወደኃላ መንሸራተት አይገባውም።
  • አዲሱ ትውልድም ለመጪው ትውልድ ፍርሃትን እና አምባገነንነትን ማውረስ የለበትም። 
  • የሕገ መንግስቱ አንቀፅ 30 ማንኛውም ሰው በሰላማዊ መንገድ ሰላማዊ ሰልፍም የማድረግ መብት እንዳለው ይገልፃል።
  • ይህ ግን በተለያየ መንገድ ተሸራርፎ ሕጉ ስለመፃፉም ለመርሳት የሚዳዳቸው አለቆች በዝተውብናል።
  • ዜጎች ሃሳባቸውን በነፃ የመግለፅ መብታቸው ይከበር!
  • የሕገ መንግስቱ አንቀፅ 30 ይከበር!


ሚያዝያ 30፣1997 ዓም የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ (ቪድዮ)

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...