Thursday, May 9, 2013

የሕገ መንግስቱ አንቀፅ 30 ይከበር! የዲሞክራሲ መብታችን ወደፊት እንጂ ወደኃላ መንሸራተት አይገባውም-ሚያዝያ 30፣1997 ዓም የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ (ቪድዮ)

ሚያዚያ 30፣1997ዓም ዕሁድ አዲስ አበባ ምናልባትም በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የ ዲሞክራስያዊ ለውጥ የሚጠይቅ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጎ ነበር። በሚልዮን የሚቆጠር ሕዝብ በሰላም ወጥቶ በሰላም የገባበት- ሁሉም ነገር ካለ አንዳች እረብሻ የተጠናቀቀበት ታሪካዊ ሰልፍ ነበር።ይህ ሰልፍ ከተደረገ እነሆ ስምንት አመታትን አሳለፈ።
  • የዲሞክራሲ መብታችን ወደፊት እንጂ ወደኃላ መንሸራተት አይገባውም።
  • አዲሱ ትውልድም ለመጪው ትውልድ ፍርሃትን እና አምባገነንነትን ማውረስ የለበትም። 
  • የሕገ መንግስቱ አንቀፅ 30 ማንኛውም ሰው በሰላማዊ መንገድ ሰላማዊ ሰልፍም የማድረግ መብት እንዳለው ይገልፃል።
  • ይህ ግን በተለያየ መንገድ ተሸራርፎ ሕጉ ስለመፃፉም ለመርሳት የሚዳዳቸው አለቆች በዝተውብናል።
  • ዜጎች ሃሳባቸውን በነፃ የመግለፅ መብታቸው ይከበር!
  • የሕገ መንግስቱ አንቀፅ 30 ይከበር!


ሚያዝያ 30፣1997 ዓም የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ (ቪድዮ)

No comments:

የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል አዛዥ ኮሞዶር ጌታቸው ስዩም በምፅዋ የኢትዮጵያ የባሕር በር ላይ እጅ አልሰጥም ብለው ያፈሰሱት ደም ዛሬም በባሕሩ ዳር ላይ ይጣራል።

በአስመራ የተወለዱት የኮሞዶር ጌታቸው ባለቤት፣በአዲስ አበባ የተወለዱት ልጆቻቸው ዛሬ ላይ ሆነው የሚነግሩን አለ  ሙሉ ቪድዮውን ይከታተሉ።