ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, August 5, 2019

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ከ70 በላይ በሚሆኑ ምሁራን በ16 መስኮች ላይ ያተኮረ የመጀመሪያ ደረጃ ረቂቅ ፖሊሲዎች አዘጋጀ።

የኢዜማ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት 

ጉዳያችን/ Gudayachn
ሐምሌ 30/2011 ዓም (ኦገስት 6/2019 ዓም)
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ከ70 በላይ በሚሆኑ ምሁራን በ16 መስኮች ላይ ያተኮረ የመጀመሪያ ደረጃ ረቂቅ ፖሊሲዎች ማዘጋጀቱን ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ሐምሌ 27 እና 28/2011 ዓም በአዲስ አበባ ሆልዴይ ሆቴል ባዘጋጀው የፖሊሲ መወያያ መድረክ አስታወቀ።የኢዜማ የፓሊሲ ጥናት እና ምርምር ኃላፊ አምሐ ዳኘው የውይይቱ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት ጥናቶቹ ለኢትዮጵያ ተጨባጭ ችግሮች መፍትሄ መሆን የሚችሉ የፖሊሲ አማራጮችን ለመቅረፅ ዋነኛ ግብዓት እንደሚሆኑ ገልፀዋል። በሌላ በኩል የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)  አሁን ካለንበት በጭንቀት እና በተሰፋ የሚዋልል ሀገራዊ ሁኔታ ወጥተን ወደተረጋጋ ሥርዓት የምንሄደው በዕውቀት ላይ የተመሠረቱ ውይይቶች ብቻ መሆኑን ገልፀዋል። 

በውይይቱ ላይ እንደተገለጠው የፖሊሲ ጥናቶቹ በትምህርት፥ቴክኖሎጂና የፈጠራ ሥራ፣ ሠራተኛ እና ማኅበራዊ ዋስትና፣ ባሕል፥ ቱሪዝምና ኢኮ ሲስተም፣ የፊስካል፥ የገንዘብ እና መዋለ ነዋይ እንዲሁም የውጭ ኢኮኖሚ እና ዲያስፖራ ፖሊሲ  እና ሌሎች  መስኮች  ላይ የተጠኑ የፖሊሲ ጥናቶች ከተጠኑት ፖሊሲዎች ውስጥ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል ዜግነትን መሠረት ያደረገ የፖለቲካ ሥርዓት እና ማኅበራዊ ፍትህን መሠረት አድርገው የተሠሩት እነኝህ የፖሊሲ ጥናቶች የኢዜማ አባል የሆኑ እና ገለልተኛ ባለሙያዎች በጋራ ያጠኗቸው ናቸው። በቀጣይ ጊዜ ለውይይት የቀረበው ረቂቅ ፖሊሲው በፓርቲው አመራሮች እና በአዘጋጅ ምሁራን በዝርዝር ከተመከረበት በኋላ፤ በፓርቲው የተለያዩ መዋቅሮች ደረጃ ውይይት እንደሚካሄድበትም በውይይቱ ወቅት ተወስቷል።በመቀጠለም ከፓርቲው አባላት ጋር ከሚደረግ ውይይ በኋላ ረቂቅ ፖሊስው ስልጣን ባለው የፓርቲው አካል ፀደቆ የኢዜማ የፖሊሲ ሰነድ እንደሚሆንም ተነግሯል።

ይህ በእንዲህ እያለ ፋና እንደዘገበው የኢዜማ መሪ ፕሮፌስር ብርሃኑ የፖለሲ ዝግጅቱ የፓርቲው የምርጫ ዝግጅት አካል ይሆን ወይ? ተብለው ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፥ ምርጫው በየትኛውም ጊዜ ይካሄድ ፓርቲው ፖሊሲዎችን የማዘገጃት ግዴታው መሆኑን መናገራቸውን እና ሰለቀጠዩ ምርጫም በሰነዘሩት ሃሳብም የምርጫው ማከናወኛ ወቅት ከጊዜ ይልቅ በሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ቢወሰን የተሻለ ነው ካሉ በኃላ በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላም እና መረጋጋት መስፈኑ፣ ፓርቲዎች በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በነፃነት ለመንቀሳቀስ የሚችሉበት አውድ መኖር እና ምርጫ ቦርድ ትክክልኛ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ማረጋገጫ መስጠቱ፤ የምርጫውን መከወኛ ጊዜን የመወሰን አቅም እንዳላቸው  መግለጣቸውን ፋና ዘግቧል።
ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...