ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, May 27, 2019

በጋዜጠኞች ላይ ለሚደርሰው ጥቃት መፍትሄው - መደራጀት!

የጉዳያችን ማስታወሻ 
ግንቦት 19፣2011 ዓም (ሜይ 27፣2019 ዓም) 
=================
''ጋዜጠኝነት አንባቢዎች የታሪክ ምስክር ሲያደርግ ፣ ልብወለድ ፅሁፍ ግን ተደራሾቹ ድርሰቱን እንዲኖሩት አንድ ዕድል ይሰጣቸዋል።'' ጆን ሄርሴ 
'' Journalism allows its readers to witness history, fiction gives its readers an opportunity to live it.'' John Hersey.
=================
foto from gorjnews.ro

በያዝነው የፈረንጆቹ 2019 ዓም ''ዘ ኒዎርከር'' (The NEW YORKER) ሚያዝያ 22 ዕትም  እውቁን ጋዜጠኛ ጆን ሄርሴ የተመለከተ ፅሁፍ አውጥቶ ነበር።በእዚሁ ፅሁፉ ላይ ግለሰቡ የጋዜጠኝነት ሙያ ዘመናዊ ቅርፅ የሰጠ እንደሆነ ያትታል።ጆን ሄርሴ ''ሂሮሽማ'' በተሰኘው መፅሐፉ ነው ብዙዎች የሚያውቁት።ከላይ ይህ ጋዜጠኛ እንደማይዋሽ የገለጠበት ማስረጃ የታሪክ ምስክር እራሱ ሕዝብ መሆኑን በጥሩ አገላለጥ አስቀምጦታል።

አሁን በንኖርበት ዓለም ሕዝብን ከህዝብ፣መንግስት ከሕዝብ  እና መንግስትን ከመንግሥታት  ጋር በማገናኘት የጋዜጠኞች ሚና እጅግ ከፍ ያለ ነው። ጋዜጠኛ የህዝብ ዓይን ነው።ባለሥልጣኑ፣ነጋዴው፣ወታደሩ እና ፖሊሱ ሁሉ የሚሰራውን ካለምንም ፍርሃት ወደ አደባባይ የሚያወጣ ጋዜጠኛ ነው። ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ዘመን ከማንም ያልወገነ፣ነገር ግን ከህዝብ እና ሀገር ጋር ብቻ የቆመ ጋዜጠኛ በእጅጉ ያስፈልጋታል።

ጋዜጠኛ በየትኛውም ዓለም መንግስት እና አምባገነን ቡድኖች የሚፈሩት ትልቁ ጣኦት ነው።ጋዜጠኛ የሰሩትን ወንጀል ብቻ ሳይሆን ያሰቡትን ዕቅድ ሁሉ ስለምያጋልጥ እንደተፈራ ብቻ ሳይሆን እንደተጠቃ ይኖራል። ባደጉት ሀገሮች ሳይቀር ጋዜጠኞችን በድብቅ ማጥቃት፣በጥቅማቸው ላይ ሴራ መስራት እና እስከ ቤተሰብ የወረደ ማስፈራራት ሁሉ በጋዜጠኞች ላይ ይፈፀማሉ። እነኝህ ሁሉ ተግባራት ጋዜጠኛው የወንጀለኛ ቡድኖችን የወንጀል ሥራ ወደ ሕዝብ እንዳያወጣ ከመፍራት የሚነሱ ድርጊቶች ናቸው።

ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ላይ የአሐዱ ራድዮ ጋዜጠኛ ታምራት አበራ ከራድዮ ጣብያው ውስጥ ድረስ መሳርያ አንግበው በገቡ የኦሮምያ ፖሊሶች ተይዞ ለሶስት ቀናት ታስሮ መለቀቁ ተሰምቷል።ይህንኑ ጋዜጠኛ ሊጠይቅ የመጣው  ሌላ ጋዜጠኛም እንዲሁ ታስሮ መለቀቁ ሌላው የሳምንቱ ዜና ነው። በመጀመርያ ደረጃ ያ! የመከራ ዘመን አልፎ ይሄው አንድ ጋዜጠኛ ሶስት ቀን መታሰሩ የምናማርርበት ዘመን በመድረሳችን ብቻ እግዚአብሔርን ማመስገን ይገባል።ይህ ካለፈው ግፍ ጋር ሲነፃፀር ቅንጦት ይመስላል። ነገር ግን አይደለም። የጋዜጠኛው የታሰረበት ምክንያት ከአመት በፊት በዘገበው ጉዳይ መሆኑ እና ራድዮ ጣብያ ድረስ የታጠቁ ፖሊሶች ሄደው ማሰራቸው መልዕክቱ ቀላል አይደለም።

በአፍሪካ እያቆጠቆጡ ያሉት አዳዲስ አሸባሪ ቡድኖች እራሳቸውን በመንግስት መዋቅሮች ውስጥ አንገታቸውን እየቀበሩ የማሸበር ተግባራቸውን ሕጋዊ ሽፋን ሊሰጡት ሲሞክሩ አዲስ ክስተት አይደለም።እንደ ኬንያ እና ዩጋንዳ ለመንግስት ቅርበት ያላቸው ጠበቆች እና የፀጥታ አካላት የተቻቸውን ጋዜጠኛ በቀጥታ በመንግስት ሳይሆን የምያስጠቁት ሕጋዊ በሚመስሉ አካላት ግን በሌላ ጉዳይ እየተፈጠረ ነው።ይህንን የማሸበር ሥራ በመስራት በኢትዮጵያ አሁን ያለው መንግስት ሥራ የተጠለሉ ነገር ግን መንግስት እንደአካል ያልላካቸው የራሳቸውን ስልጣን በመጠቀም በሌላ መዋቅር ከሚሰሩት አካል ጋር እየተመሳጠሩ ጋዜጠኞችን ማሸማቀቅ ይዘዋል።ይህንን ተግባር መንግስት ባለው መውቃር ለጋዜጠኞች በቂ ጥበቃ እና ልዩ መብት እንዲሰጣቸው ማድረግ አለበት።

በጋዜጠኞች ላይ ለሚደርሰው ጥቃት መፍትሄው

ጋዜጠኞች ላይ ጥቃት በግልፅም ሆነ በስውር መፈፀም በተለይ እውነቱን በሚጋፈጡ ላይ የነበረ ነው ተብሎ የሚተው ጉዳይ አይደለም።መፍትሄ አለው። መፍትሄው ጋዜጠኞች ደረጃውን የጠበቀ በሰው ኃይል፣በሕግ ባለሙያ እና በገንዘብ የተደራጀ የሙያ ማኅበር ያስፈልጋቸዋል።ይህ ማኅበር ከየትኛውም የፖለቲካ አስተሳሰብ ያላማከለ ነገር ግን በሀገራዊ እና  ሁሉም ጋዜጠኞች ሊመሩበት በሚገባው መሰረታዊ ሃገራዊ እና የህዝብ ጥቅም ላይ የተመሰረተ መመርያ ሊኖረው ይገባል።በእርግጥ ከኢትዮጵያ አንፃር አሁን ባለው ሁኔታ ጋዜጠኛ ማን ነው? ምን መስፈርት ያሟላ ነው ጋዜጠኛ የሚባለው? የጋዜጠኞች ማኅበር በአባልነት ማቀፍ ያለበት በምን መስፈርት አውጥቶ መሆን አለበት እና የሕግ ጥበቃም ሆነ ለሚደርስባቸው የኢኮኖሚ ሆነ አካላዊ ጉዳት ከጎናቸው የሚሆነው እንዴት ነው? የሚሉት መሰረታዊ ጥያቄዎች የመለሰ ጠንካራ የሙያ ማኅበር ማቆም ወይንም የነበረውን መልሶ ማዋቀር እና ሕይወት ያለው የሚንቀሳቀስ ማኅበር ማድረግ አለባቸው። ይህ ካልሆነ ጥቂቶች ተሰብስበው በሚሰሩት የሽብር ተግባር ብዙዎች ጋዜጠኞች ከሙያው ስነ ምግባር የራቁ ይሆናሉ።የሙያ ማኅበሩ መልሶ ማንሰራራት በጋዜጠኞች ላይ አለአግባብ የማስፈራራት፣የማሰር እና የማንገላታት ተግባር የሚፈፅሙ ባለስልጣናትን አሽትቶ ደርሶ ማጋለጥ እና ማሳጣት በመቀጠልም ለፍርድ ማስቀረብ ሁሉ የሙያ ማኅበሩ ተግባር ይሆናል።ጋዜጠኞች አሁንም ተደራጁ! ቅፅራችሁን ሳታስደፍሩ በነፃነት ለኢትዮጵያ ለመናገር ቅድምያ ጠንካራ ማኅበር ይኑራችሁ።ያን ጊዜ ማንም አይደፍራቹም።

ጋዜጠኛው በቴዎድሮስ ሞሲሳ  (ዜማ)



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...