ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, February 19, 2018

ጉዳያችን በእንግሊዝኛ ኦድዮ በቅርቡ ሥራ ትጀምራለች።Gudayachn audio in English is coming soon!




- ለምን የእንግሊዝኛ ዜና አስፈለገ?
ለምን ኦድዮ?
የእንግሊዝኛው ዝግጅት ከአማርኛው ዜና አቀራረብ በምን ይለያል?

ጉዳያችን ከ2003 ዓም ጀምሮ በድረ ገፅ በአማርኛ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ምጣኔ ሃብታዊ እና በመጠኑ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ዜናዎች እና መጣጥፎችን ለአማርኛ አንባቢዎች አቅርባለች።በእዚህም መሰረት ከአንድ ሚልዮን የሚልቁ ኢትዮጵያውያን ገፁን የጎበኙ ሲሆን ቁጥሩ በእዚህ ዓመት የበለጠ ለማሳደግ ጥረት ይደረጋል።

አሁን ጉዳያችን ከአማርኛ ፅሁፎች ጎን የእንግሊዝኛ ኦድዮ ዜናዎች በተለይ አትዮጵያን በተመለከቱ ዜናዎች እና ጉዳዮች ባብዛኛው ኢትዮጵያን የተመለከቱ ዜናዎችን ለማቅረብ ታስባለች።

ለምን የእንግሊዝኛ ዜና አስፈለገ?

የእንግሊዝኛ ዜናው ያስፈለገበት ምክንያት ስለሶስት ምክንያት ነው።

1ኛ) ስለ እኛ እኛ መናገር ስላለብን : -

የኢትዮጵያ ጉዳይ ለቀረው ዓለም መንገር ያለብን እኛው መሆን አለብን።ሌሎች ስለኛ በተናገሩ ቁጥር ከባህላችን፣ታሪካችን እና ማንነታችን አንፃር ብዙ የማይረዱት ጉዳይ ስላለ ሌሎች በሚገባ የእኛን ጉዳይ ማቅረብ ያለብን እኛው ነን።

2) በውጭ የተወለዱ እና በማደጎ የመጡ  ትውልደ ኢትዮጵያን ስለ ሀገራቸው መረጃ እንዲያገኙ ለማድረግ 
በውጭ የተወለዱ እና በማደጎ የመጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በባህር ማዶ ቀላል የሚባል ቁጥር አይደለም።ይህ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኢትዮጵያዊ ደግሞ በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎችን አይረዱም። ይህ ማለት ለኢትዮጵያ ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረግ የሚችለው የሰው ኃይል ሀብት ከመረጃ ውጭ ሆነ ማለት ነው።በተለይ እንደ ሰሞኑ የሀገራችን ጉዳይ በእየጊዜው ሲቀያየር ይህ ትውልድ ከመረጃ ውጭ ሆነ ማለት ነው።

3) ለውጭው ዓለም እራሳችንን በሚገባ አለማስተዋወቃችን 

በርካት የውጭ ሀገር ሰዎች ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ለማወቅ አብዛኛው ከኢትዮጵያዊ የሚወጡት ዘገባዎች በእንግሊዝኛ ቋንቋ ስላልሆኑ ከውጭው ዓለም ጋር ያለን ግንኙነት በሚገባው ደረጃ አይደለም።ስለሆነም የእንግሊዝኛ ኦድዮ አስፈላጊ መሆኑ ታመነበት።

ለምን ኦድዮ?

ኦድዮ የሆነበት ምክንያት የዘመኑን ተንቀሳቃሽ ትውልድ ተቀምጦ ከሚያነበው ይልቅ በመንገድ ላይ በመኪናው ውስጥም ሆነ በሕዝብ መመላለሻ ትራንስፖርት ውስጥም ሆኖ በቀላሉ በጆሮ ማዳመጫ  በመስማት መከታተል ያመቸዋል።

የእንግሊዝኛው ዝግጅት ከአማርኛው ዜና አቀራረብ በምን ይለያል?

በእንግሊዝኛ የሚቀርበው ዜና ባብዛኛው ጉዳያችን እራሷን ችላ በእራሷ የምታመጣው ዜና ላይሆን ይችላል።ሆኖም ግን በአማርኛ የሚዘገቡት ዜናዎችን ሀገርኛውን ቋንቋ ለማይረዳው ወገን መልሶ ማሰማት ጭምር እራሱ የመረጃ የማቅረቡ ሂደት አካል ነው። ከእዚህ በተለየ አቅም በፈቀደ ስለ እራሳችን ለቀሪው ዓለም እና ለአፍሪካውያን እንዲደርስልን የምንፈልገውን መልዕክት ለምሳሌ ታሪካችንን፣እምነታችንን እና ማንነታችንን የሚገልጡ በእንግሊዝኛ የተፃፉ ፅሁፎች በድምፅ  ይቀርቡበታል።
እዚህ ላይ የእንግሊዝኛው ዝግጅት ከአማርኛው በምን ይለያል? ለሚለው መልስ የሚሆነው የእንግሊዝኛው ለባዕዳንም ጭምር ስለሚደርስ ኢትዮጵያዊ ተቋሞቻችን እና እሴቶቻችን ላይ የበለጠ ጥንቃቄ ለማድረግ ይሞከራል።ለምሳሌ የውጭውን ስነ ልቦና የማይመጥኑ አገላለጦች በተቻለ መጠን ለማስወገድ እና ጨዋነት የተላበሱ ቃላት ለመጠቀም ይሞከራል።

ባጠቃላይ እራሳችንን ለቀሪው ዓለም የምንገልጥበት መንገድ በማነሱ ሳቢያ የሚጀመረው በድምፅ መረጃ ለቀረው ዓለም የማድረስ ሥራ በእናንተ አስተያየት እና ምክርም ጭምር ለፍሬ የሚያበቃ ሥራ እንደሚሆን ከፍ ያለ እምነት አለኝ።

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...