ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, September 18, 2012

ሃገርን ማዳን እራስንም ማዳን ነው !

  • የታሰሩ የ ፖለቲካ እስረኞችን ይፈቱ ማለት ብቻ ሳይሆን ከተፈቱ በኋላ ለ እስር የዳረጋቸውን ጥያቄ መመለስ አለመመለሱ ነው ዋናው ቁም ነገር፣
  • ሃገርንም እራስንም ለማዳን ኢህአዲግም ሆነ አንዳንድ የ ኢህአዲግን ፖሊስ የሚቃወሙም ዋናውን ነገር እየዘነጉ በ ንዑስ ጉዳዮች ላይ ሲያተኩሩ ማየት እጅግ አሳሳቢ ነው፣
  •  የ ኢትዮጵያ ሕዝብ ከ አድዋ መጣ፣ከ ጅጅጋ፣ከ ጎጃም መጣ ከ አሳይታ የ ፖሊሲው ማዕቀፍ ሳይስተካከል ኢህአዲግ ምንም ለውጥ ሊያመጣ እንደማይችል ይረዳዋል፣
  • የሀገራቸውን አንድነት መሰረት ያደረጉ መሰረተ ሰፊ (Broad-based) እና ሀገር ወዳዱን፣ ምሁሩን  እስከ ገበሬ ያሳተፉ  ፓርቲዎች በ ሩቅ ምስራቅ ሃገራት ለ ሀገራቸው ልማት ታምር መስራት መቻላቸው የ ዘመኑ ክስተት ነው።


ባለፈው ቅዳሜ ከቀትር በሁዋላ ኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር አስራ አንድ ሰዓት ገደማ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝን ኢህአዲግ ምክር ቤት ድርጅቱ ሰብሳቢነት መምረጡን ሰበር ዜና ድህረ ገፆች ተረዳሁ በጎ ነገር ለሀገራችን ቢመጣ የማይወድ ማን አለ? ፖለቲካ ንትርኩ ሁሉ አንዲት ቀን እርቅ ቢጠናቀቅ የማይሻ ማን አለ? ችግሩ ግን መልካም ጊዜ ይሆናል ብሎ በተስፋ መኖር ?ወይስ እየሄድን ያለንበትን አደጋ እርግጡን በማውራት እውነታው ጋር እራስን ማስታረቅ? ጥያቄው ይህ ነው።እውነት ነው። አለፈው ቅዳሜ ወዲህ ባሉት ሶስት ቀናትም የተለያዩ አስተያየቶች መሰንዘራቸውን ቀጥለዋል።ግማሹ ኢህአዲግ '' ሰው ለውጥ አደረገ'' ሲል የተቀረው ''ምንም ለውጥ የለም አቶ ሃይለማርያም 'ጥርስ የሌለው አንበሳ ነው' ''ይላል። ሌላው''ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ ፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ መሪአገኘች''ሲል የተቀረው '' ከደቡብ መሆኑ ስልጣን ክፍፍል በጎ ነው ይላል።''የእኔ አይነቱ ደግሞ ወደ ደርግ-መሰል የረቀቀ አስተዳደር የመግብያ ምዕራፍ ላይነን እላለሁ።አቦይስብሐትግን በፓልቶክባደረጉትገለፃላይእንዲህ ብለዋል ''እየተደዋወሉ ( ኢህአዴጎችማለት ነው) እንኳንደስ አለን!ትግሉፍሬ አፈራ! አማራም ሆነ ኦርቶዶክስ ያልሆነ መሪ መምጣቱ ትልቅ ድል ነው እየተባባሉ ነው '' ብለዋል።
ከ ሰላሳ ዓመት በኋላም የመሪ  መመዘኛው  የመጣበት  ክልል ነውን ? 
ኢህአዲግ ከ ደርግ ጋር በ ውግያ ላይ በነበረበት ጊዜ ሁሉ ''የ ኢትዮጵያ ችግር የ ብሄር ችገር ነው የ ገዢው መደብ መወገድ ብቻ ሳይሆን የ ፖለቲካው ስልጣን ብሄርን እና ቋንቋን መሰረት ማድረግ አለበት አለ። በመሰረቱ የ ብሔር ጥያቄ የችግሮች ቁልፍ መፍቻ ነው የሚለው የ ሶሻልስቱ ዓለም ስሙ በገነነበት ወቅት በ 1970 ዎቹ እአአ የተፈጠሩ የ ፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ ፋሽን ስለነበር ያኔ መነሳቱ ላይደንቅ ይችላል። የሚደንቀው ከ ሰላሳ አምስት ዓመት በኋላም ዛሬም ድርጅቱ ሰብሳቢውን ሲመርጥ እና ለ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሲያቀርብ የሚኩራራበት የመረጠውን ግለሰብ ችሎታ፣ልምድ፣ታማኝነት ከመጥቀስ ይልቅ የድርጅቱ አንጋፋ መስራች እና  በ አንዳንዶች ዘንድ '' የ ኢህአዲግ ፈጣሪ ኢንጅነር'' በተባሉት አቦይ ስብሐት ዘንድ ስለተመረጡት አቶ ሃይለማርያም የሚነገረው ክልላቸውን  እንደዋና መስፈርት ከመጠቀሱ በላይ '' ከ ሃሜት ዳንን'' በሚል ስሜት ትልቁ ድል ተብሎ የተወሳው''  ከ  እገሌ ክልል ሳይሆን ከ እገሌ መሆኑ ይህን ሃይማኖት የሚከተል ሳይሆን ያኛው መሆኑ'' መባሉ አሳፋሪ አነጋገር ብቻ ሳይሆን የድርጅቱን ታላቅ ዝቅጠት ያሳያል።

ሀገር አቀፍ ፖሊሲ  ያድናል ክልል አቀፍ ፖሊሲ  ይገላል

ኢህአዲግ ብቻ አደለም ብዙ የኢህአዲግን ስሜት የማይጋሩ ሰዎችም በሚሰጡት አስተያየት የ አቶ ኃይለማርያምን ክልል በመጥቀስ ብቻ  የተሻለ ነገር ይመኛሉ። መመኘት ጥሩ ነው። ምኞትን ግን በማስረጃ ማስደገፍ  ሌላ ነገር ነው።ኢህአዲግም የ እነኝህን ሰዎች ስሜት እያረገበ ለውጥ እንደመጣ መንገሩ አስገራሚ ነው። አንዳንዶች እዚህ ላይ ''ትንሽ ቸኮልክ ገና ምኑ ተያዘ እና'' ነው የሚሉ እንደሚኖሩ እረዳለሁ። በ እኔ አመለካከት ኢህአዲግ ለውጥ ያመጣል ብዬ ትንሽ የተስፋ ውልብታ ውስጥ የገባሁት አቶ መለስ ከተቀበሩ እስከ ጳጉሜን ወር ፍፃሜ ድረስ ነበር። የ ፍትህ  ጋዜጣ አዘጋጅን በድንገት መፍታት የ ነገሩ ድንገተኝነት '' አሁንስ በቃን ይህን ሕዝብ ስንት ጊዜ አንገላታነው? በጎ መስራት ለ እራስ ነው ክፉም እንዲሁ'' የሚል ሃሳብ ነገሰ ብዬ በጣም ተደስቼ ነበር። ቀጥሎ የነበረው ማን እንደሾማቸው ያልታወቁት የ ጦር ሹማምንት ጉዳይ ግን ፖለቲካውን ተረዳሁት ላለ ሰው ቀላል የሕግ አፈፃጸም ብቻ አይደለም የ ቡድን ስራው ያለ መሆኑን አመላካች ነው። ለምን ተሾሙ? የሚል ጥያቄ የለኝም። ለ አንድ ሀገር ዋስትናዋ ሕግ የተከተለ አሰራርን በማንገስ እና ባለማንገስ መሃል ግን ያለው አንደምታ ግልፅ ነው። ሚስጥራዊ  አሰራር በራሱ የ አምባገነናዊነት መሰረታዊ ባህሪ  ነው። ''ሁሉን ም ነገር ባንድ ጊዜ እንዴት?'' የሚሉትን እዚህ ላይ ማንሳት አልፈልግም ስራዬ አደጋው ታየኝ ሁሉም ሊ ታየው ይገባል ነውና።

ኢህአዲግ ምን ያድርግ?
ኢህአዲግ እኮ ብሄርን መሰረት ያደረገ ፖሊሲውን እንዲቀይር ያልመከረው የለም? ከድርጅቱ የወጡት የ ፋያናንስ እና የ ውጭ ግንኙነት ኃላፊው፣የ መከላከያ ሚንስትሩ ከሁሉም በላይ ፕሬዝዳንት አድርጎ የሾመው ሰው ሁሉ ፖሊሲውን ተቃወሙ።የትኛው ሀገር ነው የ እዚህን ያህል የ ፖሊሲ ተቃርኖ ከ እራሱ ከድርጅቱ መሃል በ እንደዚህን ያህል የ ስልጣን እርከን ያሉ ያጣጣሉት ፖሊሲ ? ይህ ትምህርት ካልሆነው ምን ትምህርት ሊሆነው ይችላል? እንደሚመስለኝ አሁን ኢህአዲግ ይህን  ወቅት የ መሰረታዊ ፖሊስ ለውጥ በማድረግ ሀገርንም ህዝብንም ማዳን የሚገባው ወቅት ላይ ነው እና የሚከተሉትን ለውጦች የማምጣት ድፍረት ካሳየ ብቻ ይመስለኛል ሕልውናውንም ሀገሪቱንም ከ ከፋ አደጋ የሚታደጋት።
1/ ከክልል መሰረት አስተሳሰብ ብሔራዊ አስተሳሰብ ላይ የተመሰረተ ፓርቲ መሆን
ይህ ሥራ ከየት ይጀመራል? ቢሉ   መልሱ  የ አባል ድርጅቶች ስምን ከመቀየር የሚል ነው። ''ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሓት)'' እስከመቼ የትግራይን ሕዝብ ብቻ ነፃ የሚያወጣ የሚል ስም ይዞ ይዘልቃል? ''ብሄረ አማራ ዲሞክራሳዊ ድርጅት (ብአዲን )'' እስከመቼ የ አማራ ግንባር ነኝ  እያለ ሲፎክር ይኖራል? የ ''ኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራስያዊ  ድርጅት (ኦህዴድ )'' እስከመቼ ለ ኦሮሞ መብት ብቻ ቆምያለሁ ይላል? ሌሎችም አንድ ላይ  ተዋህደው ይቀላቀሉ እና የ አራት ፣ አምስት ፣ ስድስት ፓርቲ ጥምረት ነው መባሉ ቀርቶ የ አንዲት ኢትዮጵያ ውሁድ ፓርቲ ሆነው ይምጡ ።የሀገራቸውን አንድነት መሰረት ያደረጉ መሰረተ ሰፊ (Broad-based) እና ሀገር ወዳዱን፣ ምሁሩን እስከ ገበሬ ያሳተፉ ፓርቲዎች በ ሩቅ ምስራቅ ሃገራት ለ ሀገራቸው ልማት ታምር መስራት መቻላቸው የ ዘመኑ ክስተት ነው። እነዚህ ፓርቲዎች ግን ብሄርን መስረት ያደረጉ አይደለም።

2/ ኢህአዲግ የሀገር ፓርቲ ከሆነ ፖሊስ አርቃቂም ነጋዴም ሊሆን አይችልም
ፖሊሲ አርቃቂ እና አስፈፃሚ ከ አፍሪካ ግዙፍ የሆነ የንግድ ተቋም ኢፈርት የተሰኘ የንግድ ድርጅት መስርቶ (ኢፈርትን አቶ ስብሐት ነጋ ከ አፍሪካ ግዙፍ የንግድ ድርጅት መሆኑን ለ አሜሪካ ራድዮ የ አማርኛው አገልግሎት መግለፃቸውን ልብ በሉ) ፍትሃዊ የ ምጣኔ ሀብት ስርዓት እንዴት ብሎ ነው በ ኢትዮጵያ የሚመጣው? ነገ የሚፀድቀውን  የንግድ ሕግ ቀድሞ ከሚያውቅ ነጋዴ ጋር ማን የ ገበያ ውድድር ይገባል።ሕግ አስፈፃሚውስ እንዴት ነው የሚቆጣጠረው? ኢህአዴግ ብዙ ጊዜ የሚ ናገረው'' በ ትግሉ ጊዜ ያፈራነው ሀብት ነው እና በሀገር ቤት መዋለ ንዋይን ማፍሰስ ምን ኃጢያት አለው? ወደውጭ አላሸሸንም '' የሚል መከራከርያ ነው።ስለ ውጭው ለጊዜው ይቆየን እና በ ሀገርቤት ግን ፖሊስ አውጭ አካል ነጋዴ ሆነ ማለት የሶሻሊስት የ አንድ እዝ ኢኮኖሚ ስርዓት በከፋ የ ሕዝቡን ባለቤትነት ባላረጋገጠ ለሙስና እና ለመጨቆኛ መልክ በተዘጋጀ መልክ ብቅ አለ ማለት ነው። ስለዚህ'' ኤፈርት '' በፍጥነት ለ ሕዝብ ሽርክና ተሸጦ ከ ፖለቲካው እና የወታደራዊ ኃይል ከያዙት ኃይሎች መላቀቅ አለበት።
ከላይ ከተጠቀሱት ሁለቱ መሰረታዊ ለውጦች ባሻገር ሌሎቹ ኢህአዲግ ተቀየረ የሚያሰኙት ነጥቦች:-
  • የፍትህ አካሉ ፍፁም ነፃ የሆነ ማድረግ፣
  • የ ጦርሃይሉን ተዋፅኦ ፍትሃዊ እና ከፓርቲ ታዛዝነት ወደ የ ሕዝብ ሀብትነት መቀየር፣
  • የመገናኛ ብዙሃንን ነፃነት ማረጋገጥ፣
  • አጠቃላይ እርቅ እና ምህረት በታመነ እና ዋስትና በሚሰጥ መልክ ማወጅ፣
  • ባለፈው የሀገሪቱ ታሪክ ላይ የሀገር አንድነትን፣የ ሕዝቡን መተማመን፣ነፃነት እና ፍትህ ላይ ያተኮሩትን ሕዝብ እንዲያውቅ ለ ዛሬው የ ሀገሪቱ ማንነት ከፍተኛ ተፅኖ እንዳለው መረዳትና መጠቀም፣
  • ነፃ የ ፓርቲዎች ውድድር ማከናወን፣
  • ዘላቂ የመንግስት ስርዓት ያለን መጭው ትውልድም ሊጠቀምበት የሚችል ህገ መንግስታዊ  ማሻሻያ ማድረግ እና 
  • ይህን ሁሉ ተግባራት ለመፈፀም አስፈፃሚ አካል መሰየም እና አፈፃፅሙም ለ ሕዝብ ግልፅ በሆነ መንገድ የሚታይ በ ጊዜ የተለካ  እንዲሆን ማድረግ የሚሉት ከብዙ በ ጥቂቱ ናቸው።
             አቶ መለስ ዜናዊ እና አቶ ሃለማርያም ደሳለኝ በ ውይይት ላይ

ሃገርን ማዳን እራስንም ማዳን ነው
ኢህአዲግ ከደቡብ ሰብሳቢ በመመደቡ ለውጥ አመጣሁ የሚለው አሁንም በ ብሔር ፖለቲካ አይኑ እያየው (ከ ሰላሳ ዓመት በፊት በነበረበት አስተሳሰብ ተዘፍቆ ስለሚመለከተው  ነው እንጂ ) የ ኢትዮጵያ ሕዝብ ከ አድዋ መጣ፣ከ ጅጅጋ፣ከ ጎጃም መጣ ከ አሳይታ የ ፖሊሲው ማዕቀፍ ሳይስተካከል ኢህአዲግ ምንም ለውጥ ሊያመጣ እንደማይችል ይረዳዋል።ሃገርንም እራስንም ለማዳን ኢህአዲግም ሆነ አንዳንድ የ ኢህአዲግን ፖሊስ የሚቃወሙም  ዋናውን ነገር እየዘነጉ በ ንዑስ ጉዳዮች ላይ ሲያተኩሩ ማየት እጅግ አሳሳቢ ነው። አንዳንዶችም ኢህአዲግ ሊጠየቅ የሚገባውን ዋናውን ጥያቄ  በአንዳንድ እርምጃዎች ሲዘነጉ ማየት አሳዛኝ ነው።ስለዚህም ተቃዋሚዎችም ሊያተኩሩበት የሚገባው ዋና ዋና የ ፖሊሲ  እና የ ህገ መንግስታዊ ማሻሻያ ጉዳዮች ላይ እንጂ በ እለት እለት ተግባራት ላይ ብቻ መሆን የለበትም።ለምሳሌ :-
  • የታሰሩ የ ፖለቲካ እስረኞችን ይፈቱ ማለት ብቻ ሳይሆን ከተፈቱ በኋላ   ለ እስር የዳረጋቸውን ጥያቄ መመለስ አለመመለሱ ነው ዋናው ቁም ነገር፣
  • የ ኢህአዲግ ክልልን መሰረት ያደረገ ፖሊሲ በ ሥራ ላይ በቆየባቸው እያንዳንዱ ቀናት ተጨማሪ አደጋ እየያዘ መሆኑን መረዳት፣ላልተረዱት ማስረዳት ነው ትልቁ ሥራ እና 
  • አደጋውን በጥናት በተደገፈ መረጃ በየዘርፉ ለ ህዝቡ ማስረዳት ለመፍትሔውም ከልብ መስራት የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው።
ኢህአዲግም መሪ ከ እገሌ ክልል እና እገሌ ሃይማኖት አመጣሁላችሁ እያለ የ ዛሬ ሰላሳ ዓመት በፊት በነበረ አስተሳሰብ ላይ ሆኖ  ከሚነግረን የተመረጡት ሰብሳብዬ ስብእና ፣ችሎታ፣ራእይ እና አቅም ይሄ ነው ብሎ መናገር ከ አንድ መንግስት የሚጠበቅ ትንሹ መስፈርት መሆኑን መረዳት ይገባዋል።
አበቃሁ 
ጌታቸው በቀለ 
ኦስሎ 





 

4 comments:

Teklu said...

ጌታቸው
በጣም ምርጥ ምልከታ ነው በዚሁ ቀጥል

Sosna B. said...

''ኢህአዲግም መሪ ከ እገሌ ክልል እና እገሌ ሃይማኖት አመጣሁላችሁ እያለ የ ዛሬ ሰላሳ ዓመት በፊት በነበረ አስተሳሰብ ላይ ሆኖ ከሚነግረን የተመረጡት ሰብሳብዬ ስብእና ፣ችሎታ፣ራእይ እና አቅም ይሄ ነው ብሎ መናገር ከ አንድ መንግስት የሚጠበቅ ትንሹ መስፈርት መሆኑን መረዳት ይገባዋል''
Anjete teb yale ababal.
Bertaln Gecho Hager be chigir lay hona temryalehu bilo erasun keshegotew yiliq ante 10 etif tibeltaleh.Halafinethn eyetewetah new.Thank u.

Deneke said...

"ከ አማራም ሆነ ከ ኦርቶዶክስ ያልሆነ መሪ መምጣቱ ትልቅ ድል ነው"-----The most horrifying and uninhabited philosophy.

keep on Gech

Deneke said...

"ከ አማራም ሆነ ከ ኦርቶዶክስ ያልሆነ መሪ መምጣቱ ትልቅ ድል ነው"-----The most horrifying and uninhabited philosophy.

keep on Gech

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።