ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, March 21, 2014

ኢትዮጵያዊቷ ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ በዓለም ዙርያ ካሉ 1000 ሳይንቲስቶች ውስጥ ከተመረጡት ከዓለም አምስቱ ምርጥ ሳይንቲስቶች ከአፍሪካ እና አረብ ሃገራት ደግሞ ብቸኛ ሆነው የ 2014 ዓም የዩኔስኮ 'ሎሬአል' ሽልማት አሸናፊ ሆኑ።

ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ

ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ በዓለም ላይ ካሉት አምስቱ ምርጥ ሴት ሳይንቲስቶች ውስጥ አንዷ እና በአፍሪካ እና ከአረብ ሃገራት ብቸኛ ሆነው የተመረጡ መሆናቸውን የዩኔስኮ ድረ-ገፅ ገልጧል።

ድረ-ገፁ አክሎም  የምርጫውን ሂደት ሲያስረዳ አንድ ሺህ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ኔትዎርክ አማካይነት ምርጫውን እንደሚያደርግ፣ በመጨረሻ አስራ ሁለት አባላት ባሉት ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ ማኅበረሰብ (International Scinitfic Community) አማካይነት ውሳኔ እንደሚያገኝ ያብራራል።

ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ መቀመጫውን ናይሮቢ ኬንያ ያደረገው በአካባቢ ስነ-ምህዳር ላይ የሚሰራው  International Center for Insect Physiology and Ecology (ICIPE) ዳይሬክተር ጀነራል ሆነው ይሰራሉ።

ዩኔስኮ ሽልማቱን አስመልክቶ የሰጠውን ዜና ከእዚህ በታች ባለው ሊንክ ይመልከቱ።
http://www.unesco.org/new/fileadmin/MULTIMEDIA/HQ/SC/pdf/PressR_L-OREAL_UNESCO_2014_EN.pdf

ጉዳያችን
መጋቢት 12/2006 ዓም 

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...