ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, July 12, 2023

የትግራይ ክልል ጳጳሳት የካሕኑ ዔሊን ድፍረት በታቦተ ጽዩን ፊት ለመፈጸም ቀጠሮ ይዘዋል።ከአርባ ዘመን በላይ ያገለገለውን ካሕኑ ዔሊን ከመቅሰፍ ያልተመለሰ የአምላክ ፍርድ ዛሬም በታቦቷ ፊት የሚፈጸመውን የድፍረት ኃጢአት ዝም አይልም።


  • ለሹመት ብለው የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን የከዱ፣ታቦተ ጽዮንን ከመሸጥ አይመለሱም።

=========
ጉዳያችን ምጥን
=========
የትግራይ ክልል ጳጳሳት ከቅዱስ ሲኖዶስ ፍቃድ እና እውቅና ውጪ በሕገወጥ መንገድ ኢጲስ ቆጶሳትን ለመሾም ይህንንም የድፍረት ኃጢአት በታቦተ ጽዮን ፊት በአክሱም ለመፈጸም ለሐምሌ 9 ቀጠሮ ይዘዋል። ይህንን የድፍረት ኃጢአት እንዳይፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ለማግባባት ብቻ ሳይሆን ባልተለመደ መንገድ ላላጠፋው ጥፋት ሁሉ ይቅርታ ከመጠየቅ አልፎ ቅዱስ ፓትርያሪኩ አቡነ ማትያስ መቀሌ ድረስ ሔደው ጳጳሳቱን ለማግኘት ቢሞክሩም ፖለቲከኞችን ለመቀበል መቀሌ አሉላ አባነጋ አየርማረፍያ ይጋፉ የነበሩ ጳጳሳት ቅዱስ ፓትርያሪኩ ላይ ቤተክርስቲያን ዘግተው ተደብቀው ውለዋል።

አሁን ምንም ሀተታ አያስፈልገውም።የድፍረት ጥጉ ልክ አልፏል።ታቦተ ጽዮን ጥንት የነበረችው ነች። የነበረው የእግዚአብሔር ክብርም ዛሬም አለ። ካህኑ ኤሊ ከበደሉ ባለመመለሱ የቀጣ አምላክ ዛሬም ለፍርድ በቦታው አለ።የኃጢአት ቀጠሮው እና የሚያስከትለውን ቅስፈት የት ድረስ እንደሚደርስ የምናየው ነው።

ስለሞተው አታልቅሱ ለገዛ እራሳችሁ እንጂ



No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...