Wednesday, July 12, 2023

የትግራይ ክልል ጳጳሳት የካሕኑ ዔሊን ድፍረት በታቦተ ጽዩን ፊት ለመፈጸም ቀጠሮ ይዘዋል።ከአርባ ዘመን በላይ ያገለገለውን ካሕኑ ዔሊን ከመቅሰፍ ያልተመለሰ የአምላክ ፍርድ ዛሬም በታቦቷ ፊት የሚፈጸመውን የድፍረት ኃጢአት ዝም አይልም።


  • ለሹመት ብለው የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን የከዱ፣ታቦተ ጽዮንን ከመሸጥ አይመለሱም።

=========
ጉዳያችን ምጥን
=========
የትግራይ ክልል ጳጳሳት ከቅዱስ ሲኖዶስ ፍቃድ እና እውቅና ውጪ በሕገወጥ መንገድ ኢጲስ ቆጶሳትን ለመሾም ይህንንም የድፍረት ኃጢአት በታቦተ ጽዮን ፊት በአክሱም ለመፈጸም ለሐምሌ 9 ቀጠሮ ይዘዋል። ይህንን የድፍረት ኃጢአት እንዳይፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ለማግባባት ብቻ ሳይሆን ባልተለመደ መንገድ ላላጠፋው ጥፋት ሁሉ ይቅርታ ከመጠየቅ አልፎ ቅዱስ ፓትርያሪኩ አቡነ ማትያስ መቀሌ ድረስ ሔደው ጳጳሳቱን ለማግኘት ቢሞክሩም ፖለቲከኞችን ለመቀበል መቀሌ አሉላ አባነጋ አየርማረፍያ ይጋፉ የነበሩ ጳጳሳት ቅዱስ ፓትርያሪኩ ላይ ቤተክርስቲያን ዘግተው ተደብቀው ውለዋል።

አሁን ምንም ሀተታ አያስፈልገውም።የድፍረት ጥጉ ልክ አልፏል።ታቦተ ጽዮን ጥንት የነበረችው ነች። የነበረው የእግዚአብሔር ክብርም ዛሬም አለ። ካህኑ ኤሊ ከበደሉ ባለመመለሱ የቀጣ አምላክ ዛሬም ለፍርድ በቦታው አለ።የኃጢአት ቀጠሮው እና የሚያስከትለውን ቅስፈት የት ድረስ እንደሚደርስ የምናየው ነው።

ስለሞተው አታልቅሱ ለገዛ እራሳችሁ እንጂ



No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...