ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, July 8, 2023

አቡነ ሰላማ ያከበሩትን፣የቀደሙ የአክሱም ነገስታት ያልተዳፈሩትን የቅዱስ ሲኖዶስ ክብር እያቃለሉ በአቡነ ሰላማ ስም የሚነግዱቱ የትግራይ ጳጳሳት ድፍረት ቅስፈት እንዳያመጣ ያሰጋል።የትግራይ ገዳማት ህገወጦቹን ጳጳሳት ሊገስጹ ይገባል።


በትግራይ ጳጳሳት በህገወጥ መንገድ እየተዟዟረ የሚገኘው ኢጲስ ቆጶስነት ለመሾም የምትፈልጉ መነኮሳት ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 3 ተመዝገቡ የሚለው የጉድ ማስታወቂያ።



=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በዓለም ቀደምት ክርስትናን ካስፋፉት አብያተክርስቲያናት ቀዳሚዎቹ ውስጥ ነች። ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባው ከእርገት በኋላ በዓመቱ በ 34 ዓም በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ አማክይነት መሆኑን በመጽሐፍ ቅዱስ ሐዋርያት ሥራ ምዕ 8 ላይ የተጻፈ ነው። ኢትዮጵያ ክርስትናን በጃንደረባው አማካይነት ብትቀበልም በብሔራዊ ደረጃ የታወጀው ግን በ4ኛው ክ/ዘመን ነበር። የመጀመርያው ጳጳስ ደግሞ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ነበሩ።

አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በሦስተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ በሕዳር 26/ 245 ዓ.ም ከአባታቸው ቅዱስ ምናጦስና ከእናታቸው ቅድስት ማርያም ሰናይት በጢሮስ /ግሪክ/ ተወለዱ። የመጀመሪያ ስማቸው ፍሬምናጦስ ይባላል። አቡነ ሰላማ የ12 ዓመት ልጅ እያሉ ሜሮጵዮስ የተባለ ነጋዴ /ፈላስፋ/ ይዟቸው ወደ አገራችን በእግዚአብሔር ፈቃድ መጣ። ከእርሱም ጋር ኤድስዮስ የተባለም አብሮት እንደነበረ ይታወቃል። እነዚህን ሁለት ወጣቶች አስከትሎ የመጣው ሜሮጵዮስ በቀይ ባሕር አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች በጣሉለት አደጋ በዚሁ እንደ ሞተ ታሪክ ይነግረናል። ፍሬምናጦስና ኤድስዮስ ግን በወቅቱ የአክሱም ንጉሥ የነበረው ንጉሥ ታዜር ጋር አድገዋል። ንጉሡ በአእምሮ መብሰላቸውን ተመልክቶ ፍሬምናጦስ በጅሮንድ ኤድስዮስም ጋሻ ጃግሬው አድርጎ ሾማቸው።

ከዚያ በኋላ ንጉሥ ታዜር ሲያርፍ ወደ ፈለጉበት እንድሄዱ ነፃ ስለተለቀቁ ኤድስዮስ ወደ አገሩ ተመልሶ ሄዷል። አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ግን በጨለማ የሚኖረውን ሕዝብ ትቼ ወደ አገሬ አልመለስም በማለት እንደቀሩ ታሪክ ያስረዳናል። 

በዚያን ጊዜ በአገራችን ኢትዮጵያ ስርዓተ ንስሐ፣ ስርዓተ ጥምቀት፣ ስርዓተ ቅዳሴ፣ ስርዓተ ቅዱስ ቁርባን የሚያከናውን ጳጳስ ስላልነበረ ይህን የተመለከቱ ነገስታት ኢዛናና ሳይዛና ጵጵስና እንዲያመጡ አባታችን አቡነ ሰላማን ወደ ግብጽ ላኳቸው። አባታችንም ወደ ግብጽ በመሄድ ስርዓቶቹን በመማር በቅዱስ አትናትዮስ አንብሮተ እድ ˝ኤጲስ ቆጶስ” ተብለው ጵጵስና ተቀበሉ። ወደ አገራችን ከተመለሱ በኋላ መጀመሪያ ነገስታት ኢዛናና ሳይዛናን አጥምቀውና አቁርበው አብርሃ ወአጽበሃ በማለት ስመ ክርስትና ሰጧቸው። በመቀጠልም በመላው አገራችን እየተዘዋወሩ በማስተማር ስርዓቱን ፈጽመዋል። 


ዛሬ በአቡነ ሰላማ ስም እየተነገደ ነው።አቡነ ሰላማ ኢጲስቆጶስነትን ለመቀበል በሱዳንና ግብጽ በረሃ ተንከራተው ሹመቱን ይዘው መጡ እንጂ እንደየዘመኑ በስማቸው እንደሚነግዱባቸው የትግራይ ጳጳሳት በጉልበት እና ፍጹም ትዕቢት በተሞላበት መንገድ ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና እና ፈቃድ ውጪ አልሄዱም።የዘመናችን የትግራይ ጳጳሳት ግን ኢጲስ ቆጶሳት ለመሾም የምትፈልጉ ተመዝገቡ የሚል ማስታወቂያም እስከማውጣት ተደርሷል የሚል ዘገባም በማኅበራዊ ሚድያ ሲዘዋወር ታይቷል። አቡነ ሰላማ በስማቸው እየተነገደ ፍጹም ድፍረት ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ለህወሃት አመራር የሚታዘዙት የትግራይ ጳጳሳት ህገወጥ ድርጊት ለበለጠ ቅስፈት እንዳይዳርግ በእጅጉ ያስፈራል።


በትግራይ ጳጳሳት እየሄዱበት ያለውን የተሳሳተ መንገድ ለመመለስ ቅዱስ ሲኖዶስ ብዙ እርቀት ከመሄድ አልፎ፣ቤተክርስቲያን ይቅርታ ጠየቀች የሚል ዜናም ተሰምቷል። አንድ የትግራይ አባት ይህንን ሰምተው ምዕመን ቤተክርስቲያንን ይቅርታ ይጠይቃል እንጂ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ነው ምዕመንን የምትጠይቀው? በማለት የጉዳዩን ተገላቢጦሽነት ገልጸውታል።እየሆነ ያለው መንፈሳዊነት ሽታ የሌለው ከቅሌት ያለፈ በፈጣሪ ላይ የሚደረግ ድፍረት ነው።አሁን የትግራይ ገዳማት አስተዳዳሪዎች ምን ይላሉ? የመገናኛ ብዙኃን በጳጳሳቱ ሕገወጥ አካሄድ ላይ ምን ይላሉ? የህወሃትን ማስፈራራት አሸንፈው የጳጳሳቱን ድርጊት የሚያወግዙ ገዳማውያን እነማን ናቸው? ይህ የመገናኛ ብዙኃኑ ሊያሰሙን እና ሊያሳውቁን የሚገባ ቀዳሚ ተግባር ነው።

===============///==============





No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...