ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, April 4, 2019

የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ ፣ በኦስሎ ያደረገው ሕዝባዊ ስብሰባ ጭብጥ

የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ ለመጋቢት 21/2011 ዓም ስብሰባ ከወር በፊት የለቀቀው ማስታወቂያ 
ETIOPISK FELLES FORUM I NORGE (Ethiopian Common Forum in Norway) meeting held in Oslo, Norway on March 30/2019.

ጉዳያችን / Gudayachn
መጋቢት 27/2011 ዓም (አፕሪል 5/2019 ዓም)
==============
የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ ባሳለፍነው ቅዳሜ መጋቢት 21/2011 ዓም  በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋዎቹና ተግዳሮቶቹ በሚል ርዕስ በኖርዌይ ዋና ከተማ በኦስሎ በሚገኘው የእንስሳት ሕክምና ምርምር ማዕከል (Veterinærhøgskole) በጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ ውይይት አድርጎ ነበር። በውይይቱ ላይ ከኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በኖርዌይ፣በፖለቲካ ድርጅት አመራርነት፣በኖርዌይ የሴቶች ማኅበር፣የኖርወጅያን ምክር ቤት ለአፍሪካ እና ምሑራን ተገኝተውበታል።

በውይይቱ ወቅት በርካታ ጉዳዮች ከመነሳታቸው አንፃር ሃሳቦቹን በተወሰኑ ነጥቦች ጨምቆ ማቅረብ ብዙ ሐሳቦች እንዲደበቁ ስለሚያደርግ ከተሳታፊዎች የተነሱትን ነጥቦች እንደወረዱ (በዘጋቢው ያልተተነተነ ጥሬ መረጃ ) ማቅረቡ በተለይ ለለውጡ ኃይልም በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ምን እያለ እንደሆነ አንድ ግብዓት ሊሆን ይችላል።ስለሆነም በተሳታፊዎች የተባሉትን እንደሚከተለው ለመዘርዘር እሞክራለሁ።



  • በኢትዮያ የሚድያ ችግር አለ።የሚያርቅ ሚድያ ማግኘት ችግር ሆኗል ፣
  • በፖለቲካ ትንታኔ ላይ ድፍረት መብዛቱ እና ሁሉም ካለሙያው እየገባ መፈትፈቱ አንዱ ችግር ነው ፣
  • ዶ/ር ዓቢይ ኢትዮጵያን ከስሟ ጀምሮ ከዘመናት በኃላ በማንሳቱ ከፍ ያለ ክብር እንሰጠዋለን፣
  • ከስር ያለው የቀድሞው የህወሓት (ኢህአዴግ) መዋቅር አለመነሳቱ ዋናው የፀጥታ ችግር ነው፣
  • አክራሪዎች ሀገር እያጠፉ ያሉት በተከፈተው የዲሞክራሲ ቀዳዳ ነው፣
  • ዶ/ር ዓቢይ አንዳች የተደበቀ አጀንዳ አላቸው የሚል ግምት የለንም።ለእዚህም ማስረጃው እስካሁን ከመጀመርያ ጀምሮ ያለው ቃላቸው አለመቀያየሩ እና ወጥ መሆኑ ነው፣
  • የቡራዩ አደጋ አንድ የትግል አቅጣጫ አስቀያሪ ሆኗል።ለፅንፈኛው አካል ዕድል ሰጥቷል፣
  • ለውጡን የሚጎዳ አንዳችም ነገር እንዳይፈፀም መከላከል አለብን፣
  • በፅንፈኛው እና በለዘብተኛው መሐል መሃል ሆኖ የኢትዮጵያን ታላቅነት የምሰብከው አካል ቦታ እያጣ ነው ፣
  • ዲያስፖራው ሀገር ቤት ባለው ፖለቲካ እንዴት ተደራሽ እንደሚሆን ማሰብ አለበት።ለምሳሌ በምርጫው ሂደት ታዛቢ የመላክ መብት አለው፣
  • ህወሓት አሁንም ያልሞት ባይ ተጋዳይ ሥራ በሶስት መንገድ እየሰራ ነው። እነርሱም: - 1ኛ) የጎሳ ድርጅቶችን በማብዛት 2)ተቃዋሚዎችን የለዘቡ እንዲሆኑ ማቅረብ እና 3)በሶሻል ሚድያ ላይ መስራት የሚሉት ናቸው።
  • እንዴት ሰው አውሮፓና አሜሪካ እየኖረ የዘር ፖለቲካ ያራምዳል? አንድ ተሳታፊ የጠየቁት።
  • The silence majority የሚታወከው በጥቂት noise ፈጣሪ ነው፣
  • መጪው ምርጫ በሚገባ መሄዱን ለማረጋገጥ በውጭ ያለው ማኅበረሰብም መወያየት አለበት፣
  • አሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ኢትዮጵያ የለችም ከሚል ፅንፈኛ ጋር ነው።ይህም በራሱ ሶስት ተግዳሮቶች ይዞ መጥቷል። እነርሱም - ማለቂያ የሌለው የፅንፈኛ ሁሉን የእኔ የሚል ጥያቄ፣በትልልቆቹ ብቻ ሳይሆን በአናሳዎች ውስጥ ያሉ የጎሳ ግጭቶች እና እነርሱን ተከትሎ የሚመጣው የከፋ ድኅነት ናቸው፣
  • በኢትዮጵያ ኢምባሲ በኩል ያለውን አሰራር ትክክለኛ እና ዘርን ያልተከተለ መሆኑን የመቆጣጠር ሥራ የዲያስፖራውም ጭምር ነው፣
  • ፅንፈኛ እያልን የምንጠራው አካል ጋር የተቀላቀሉትን ጊዜ ሰጥቶ መስማት እና በማወያየት ወደጤነኛ ፖለቲካ ማምጣት ያስፈልጋል።የናይጀርያው ''ቦኮሃራም'' ወደ ሰላማዊ መንገድ ለማምጣት የተሄደበት አካሄድ በተሞክሮነት ቀርቧል፣
  • የኖርዌይ መንግስት በኢትዮጵያ ያሉትን የፅንፈኛ እንቅስቃሴዎች ለማጥናት ከፍተኛ በጀት መድቦ እያጠና ነው፣
  • ወጣቱን ዝም ብሎ መውቀስ ይታያል።ከእዚህ ይልቅ ወጣቱን የተማሩት ቀረብ ብለው ማስተማር ነበር የሚገባቸው፣
  • ብዙዎች ኢትዮጵያ እንላለን እንጂ ቅንነት የጎደለው ፖለቲካ ነው የምናራምደው እንታረም፣
  • በጎሳ ፖለቲካ አንዳንዶች ከወያኔ ያልተለዩ ናቸው።አውሮፓ እና አሜሪካ እየኖሩ የጎሳ ፖለቲካ ማራመድ ጠነኛነት አይደለም፣
  • ለውጥ ቀስ እያለ ነው የሚሞቀው።ብዙ ስለሆን ፍላጎታችን በእዚያው መጠን ይለያያል እና ትግስት ያስፈልጋል፣
የሚሉ እና ሌሎች ሃሳቦች ተሰንዝረዋል።በመጨረሻም የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ ላለፉት አራት ዓመታት በአዲሱ ሥራ አስፈፃሚ አስተባባሪነት በተዘጋጁት የውይይት መርሐግብሮች ላይ ሶስት ግብዓት ብቻ ማለትም የአስተባባሪዎች ጊዜ፣ዕውቀት እና ነፃ የመሰብሰብያ አዳራሾችን በማፈላለግ ካለ ምንም የገንዘብ ወጪ እና ድጋፍ ሲያዘጋጅ መቆየቱ ተነግሮ ወደፊት ስራውን በተሻለ መንገድ ለማቀላጠፍ ሌሎች ምሁራን ለማሳተፍ ተከታታይ ውይይቶች ማድረጉን እና የጋራ መድረኩ ርዕይ፣ተልዕኮ እና መዋቅር በበለጠ ደረጃ የማደራጀት ሥራ በመስራት መሆኑ ለተሰብሳቢዎቹ ተጠቅሶ ስብሰባው ከምሽቱ 12 ሰዓት ተኩል ላይ ተፈፅሟል።



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...