ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, August 6, 2017

ሃዘን ጎሳ የለውም።ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው።አባታቸውን፣እናታቸውን ወይንም ልጆቻቸው ከተገደሉባቸው ጋር አብረን እንዘን።

ጉዳያችን/Gudayachn 

ኢትዮጵያ ላለፉት አርባ ዓመታት የፖለቲካ ስልጣን  ለማስጠበቅ ሲባል ብቻ የመብት ጥያቄ ያነሱ ሁሉ በአደባባይ ሲገደሉ ኖረዋል።በህወሓት የሚመራው መንግስት ስልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ የኢትዮጵያውያን እንባ አልቆመም።በተለይ ባለፉት 10 ወሮች ውስጥ በአስር ሺዎች ወደ እስር ቤት ሲጋዙ ብዙ መቶዎች (ቁጥሩ ከእዚህም እንደሚልቅ ይታመትናል) በአደባባይ በስርዓቱ ወታደሮች ተገድለዋል።በጎንደር፣ነቀምት፣አምቦ፣ባህርዳር፣አዲስ አበባ፣ኮንሶ፣ቴፒ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ቤተሰብ ሃዘን ላይ ነው።

ነገ ነሐሴ 1፣2009 ዓም በባህርዳር ከተማ ልክ የዛሬ ዓመት ባዶ እጃቸውን የመብት ጥያቄ ባነሱ ነዋሪዎች ላይ ጨካኞቹ የስርዓቱ ወታደሮች እና በጎሳ ስሜት እራሳቸውን  የተበተቡ ታጣቂዎች ከኮንደምንየም ቤቶች መስኮቶች ላይ ሁሉ በማድፈጥ በ60 ደቂቃዎች ውስጥ ከ50 ያላነሱ የከተማው ነዋሪዎች እንደቅጠል የረገፉበት ቀን ይታሰባል።በባህር ዳር ከተማ ሥራ የማቆም ጥሪ የተጠራ ሲሆን ጉዳዩ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊንም የሚመለከት ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው።
ሃዘን ጎሳ የለውም።ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው።አባታቸውን፣እናታቸውን ወይንም ልጆቻቸው ከተገደሉባቸው ጋር አብረን እንዘን።በኢትዮጵያ የትኛውም ክፍል በግፍ በአገዛዙ ሕይወታቸው የተቀጠፈውን ሰማዕታት እንዘክራቸው።

ቪድዮ:  በፕሮፌሰር አሽናፊ ከበደ “እረኛው” የተሰኘው በመሳርያ ብቻ የተቀናበረ ሙዚቃ። 
                

ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments: