ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, June 23, 2012

ኢትዮዽያን ለማጥፋት ኦርቶዶክስን ማጥፋት -''የተሃድሶ'' ቅሰጣ

የ ኢትዮዽያ ቤተ ክርስትያን የ ኢትዮዽያን ብቻ ሳይሆን የ ዓለም አሻራ የሚታዩባት ለመሆንዋ ባዕዳንም የመሰከሩላት ነች። የ ቤተ ክርስትያን መታወክ የሃገር የጸጥታ ችግር ብቻ ሳይሆን ኢትዮዽያን እንደ ሃገር እንዳትቀጥል ለማድረግ ቁልፍ ስራ እንደሆነ የተረዱ የ ኢትዮዽያ ጠላቶች ተግተው እየሰሩበት ነው።ለእዚህም ብዙ ማስረጃ ማቅረብ ይቻላል። አንዱ ማሳያ እና አይነተኛ መሳርያ ሆኖ የቀረበው እራሱን በግልጽም ሆነ በስውር ''የ ተሃድሶ እንቅስቃሴ'' እያለ የሚጠራው አንዱ  ነው።
የቤተ ክርስትያንን መሰረተ እምነቷን ለመናድ ምዕመኗን በጥርጥር ትምህርት ለመበረዝ፣ የቤተክርስትያን በሆኑት ነገሮች ሁሉ ላይ ቸልተኛ እንዲሆን፣ቅዳሴዋን፣በማሕሌት አምላኳን ማመስገኗን እና የነበረ ስርዓቷን ቀስ በቀስ ለመናድ ተንኮል በተመላበት ትምህርት፣የ ዘፈን ቃና ባለው እና መሰረተ ዕምነትን የናደ ስንኝ በያዘ መዝሙር መሰል ''መዝሙር''  በተደራጀ መልክ ማወክ ስራዪ ብለው ይዘውታል። ከሁሉም ከሁሉም ቤተ ክርስትያንን እናድሳለን ብለው የተነሱ ወይንም ከትምህርት ማነስ እናድሳለን ላሉቱ ሳያውቁ እያገለገሉ ያሉት መሰረታዊ መለያቸው ምን ያህል ስለ ተዋህዶ ቢናገሩ ስለሚሉት ሁሉ እንደማያምኑበት በ አንድም ሆነ በሌላ በስራቸው እና በትምህርታቸው ይታወቃሉ። ''ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ'' እንዲል::

ጉዳያችን ይህ ትልቅ ሃገራዊ አንደምታ ያለው ጉዳይ በኢትዮዽያ የ ሃይማኖቱ ተከታይ ባልሆኑትም ሁሉ ላይ በተዘዋዋሪም የ እራሱ አንደምታ ስላለው  የ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ያልሆኑም  ከ ሃገር ፍቅር አንጻርም ቢሆን ጉዳዩን ሊረዱት ብሎም ለሃገሪቱ የነበረ ቅርስ መጠበቅ የ እራሳቸውን ሃገራዊ ድርሻ ሊወጡ ይገባል ብላ ታምናለች።ይህ ብቻ አይደለም ለተለያየ ፖለቲካዊ ጥቅም ሲሉ ከ እዚህ አፍራሽ አስተሳሰብ ጋር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እያገዙ ያሉ ቆም ብለው ማሰብ ካለባቸው ጊዜው ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው። ''ሃይማኖት የ ህዝብ ስስ ብልት ነው'' እና::

ይህንን ሃምሳ አራት ደቂቃ የፈጀ ከ ቀሲስ ዶክተር መስፍን ተገኝ ጋር'' ብስራት'' ከተሰኘ ራድዮ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ ስለ ''ተሃድሶ''ሃገራዊ  ችግር ምንነት በትክክል የሚያመላክት ይመስለኛል። ጊዜ ወስደው ያድምጡ።




ቀሲስ ዶክተር መስፍን ተገኝ
vidio source=Deje selam sep.23,2011 (''ሊያዳምጡት የሚገባ ትምህርታዊ ቃለ ምልልስ'' http://www.dejeselam.org/2011/09/blog-post_23.html)

3 comments:

SABEQ said...

It is very informative. I could learn a lot. It makes me clear so many things. The bad thing is that ABA PAWLOS is doing the same thing to so called Tehadso. We must must fight Aba Pawlos's act in Ethiopia Orthodox church. Thank you bloger!! keep in informing us such HAGERAWI GUDAYOCH.

Anonymous said...

በእውነት የሚገርም ታሪክ ነው።ብዙ ነገሮች እየመጡ ድቅን አሉብኝ ቀሲስ ዶክተሩ ያሉት ሁሉ እውነት ነው።ዛሬ ከቤተክርስቲያን መልስ ጓደኞቸን ሰብስቤ አሳየኋቸው። እዚህ ባለሁበት ሃገር ተመሳሳይ ችግር ገጥሞን ተፈትነንበታል። የሰንበት ትምህርት ተማሪዎች ሲነግሩን አልገባንም ነበር። ሳምንት የ ጽዋ አጣጪዎቸን አሳያለሁ።አምላክ ወጣቱን ያበርታልን።

Teklu said...

Thanks for this Getachew. In fact Tehadiso is now EOTC's greatest challenge, I think. The bad thing about it is that it is a bit a challenge for an ordinary christian to detect their deeds and final motives- Tehadiso people appear very dear to EOTC and they even claim that they think much better than millions- as they boguslly synonimize their reformistic agenda to being modern and intellectual. But for sure they will not succeed as His eyes are always on EOTC. Great is that Mahibere Kidusan and a lot other christians are really breaking their backbones- they are being exposed to the people.

Best,
Teklu
http://tekluabate.blogspot.no/

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።