ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, November 20, 2015

የዘር ማፅዳት ወንጀል በኢትዮጵያ (Ethnic cleansing crime in Ethiopia) ከአለምአቀፍ እና አህጉራዊ ሕግ አንፃር

photo -foreign policy 
በቤንሻንጉል ጉምዝ  መተከል ዞን፣መስከረም ወር ላይ ከአስራ አምስት በላይ የሚሆኑ የአማራ ተወላጆች ተገድለው አስከሬናቸው በጆንያ ታስሮ ተገኘ።ሚያዝያ ወር ላይም በጥይት ሰማንያ የአማራ ተውላጆች ካለ አንዳች ምክንያት ተረሽነዋልበቤንሻንጉል ነዋሪ የሆኑ የአማራ ተወላጆች ለኢሳት ህዳር 9/2008 ዓም በምሬት የተናገሩት። ድርጊቱ  በአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ላይ ለደረሰው የዘር ማጥፋት እና የማፈናቀል ተግባር የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በሕይወት እስካሉ ድረስ በዓለም አቀፍም ሆነ አህጉራዊ ሕግያስጠይቃቸዋል።ጉዳያችን ''ኢትዮጵያ ''የዘር ማፅዳት'' ወንጀል (Ethnic cleansing crime in Ethiopia) ከአለምአቀፍ እና አህጉራዊ ሕግ አንፃር'' በሚል ከእዚህ ቀደም 2006 ዓም ያቀረበችው ፅሁፍ እነሆ-
በዘር ወይንም በቋንቋ ሳቢያ የተለየ ህዝብን ለማጥቃት የሚደረጉ ድርጊቶች የተወገዙ ናቸው።በአለም ላይ በአምባገነኖች የግፍ ድርጊት፣በዘር ወይንም በቋንቋ ሳቢያ የተለየ ህዝብን ለማጥቃት የሚደረጉ ድርጊቶች የተወገዙ ናቸው።በእዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ ደግሞ ተግባራቸውን በረቀቀ መንገድ ሲከውኑት ማየት የተለመደ ተግባር እየሆነ መጥቷል።

በሀገራችንበአፋር፣በሱማሌ፣በኦሮሞ፣በሲዳማ፣በጋምቤላ ሰሞኑን ደግሞ በአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ላይ ተመሳሳይ በአይነቱ ግን የተለየ በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት ጀርመኖች በአይሁዶች ላይ ይፈፅሙት የነበረው  አይነትግፍ እየተፈፀመ ነው።አምና በጉርዳፈርዳ፣በጅጅጋ፣በመቱ ሲፈፀም የነበረው የአማርኛ ተናጋሪኢትዮጵያውያንን የመግፋት እና የማባረር ተግባር ዘንድሮ በቤንሻንጉል በሺህ የሚቆጠሩትን ቀያቸውን አስለቅቆ የመንገድ ዳር ተመፅዋች አድርገዋቸዋል።ድርጊቱ በግብርና ሥራ የተሰማሩትን ብቻ ሳይሆን ከወፍጮቤት ባለቤትእስከ የትልልቅ ሆቴሎች ባለቤቶች ድረስ ንብረታቸውን ትተው ካለ አንዳች ካሳ እና ውክልና የመስጠት መብት ተባረዋል። ይህ ተግባር በዓለም አቀፍ ሕግ ''የዘር ማፅዳት ወንጀል'' (ethnic cleansing) ተብሎ ይጠራል።

''የዘር ማፅዳት ወንጀል'' (ethnic cleansing) ምንድነው? 

ታህሳስ 81989 ዓም እኤአ  በተባበሩት መንግሥታት 1948 ዓም እኤአ የፀደቀውን የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀሙ ወንጀለኞችን ለመቅጣት የፀደቀውን አለም አቀፍ ሕግ 50 አመት ሲከበር በወቅቱ የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ የነበሩት ኮፊ አናን የወጣው ዘገባ ''የዘር ማፅዳት ወንጀልን'' ትርጉም እንዲህ ያስቀምጠዋል ''Ethnic cleansing has been defined as ''the elimination of an unwanted group from society,as by genocide or forced migration.'' Genocide and ethnic cleansing by Karin Becker (http://www.munfw.org/archive/50th/4th1.htm).
''የዘር ማፅዳት ትርጉም ''አንድ ያልተፈለገ ቡድንን(ህዝብን) ከሚኖርበት ማህበረሰብ ለይቶ በጅምላ መፍጀት አልያም በግድ ከመኖርያው የማፈናቀል እና ስደተኛ የማድረግ ተግባር ነው።''

የአለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች በተለይ በገዛ ሀገራቸው ተገፍተው ስደተኛ ለሆኑት (Internally displaced persons) ዜጎች አለምአቀፍ ጉዳይ ከሆነ እና ተግባሩን የሚፈፅሙት ላይ በሕግ የመጠየቅ ሂደት የሀገሮችሮች ሁሉ ኃላፊነት መሆኑን አለም ተስማምቷበታል።በ ታህሳስ 6፣2012 ዓም እኤአ ''የ ካምፓላ ኮንቬንሽን'' በመባል የሚታወቀው በገዛ ሀገራቸው ስደተኛ የሆኑ አፍሪካውያንን ላይ ትኩረት ያደረገው ጉባኤ መንግሥታት በገዛ ሀገራቸው ለተሰደዱ ዜጎች የመደገፍ፣የመንከባከብ እና ሙሉ የከለላ እና ልዩ ጥባቆት እንዲያደርጉ የሚያስገድድ ሕግ ከመውታጡም በላይ የአፍሪካ ህብረት በ ኮንቬንሽኑ መሰረት ከ 37 በላይ የሚሆኑ ሃገራት እንዲፈርሙ ሆኗል። የስደቱ መንስኤ እራሳቸው መንግሥታቱ ለሆኑባቸው ሀገሮች ግን አለም አቀፍ ሕግ የሚዳኘው ''በዘር ማፅዳት'' ወንጀል ነው።'የካምፓላው ኮንቬንሽን' ለአፍሪካ አህጉር በተለይ በጎሳ እና በዘር ላይ የተመሰረቱ መንግስታትን አደብ የሚያስገዛ የሕግ መነሻ ወደፊት እንደሚሆን ይጠበቃል።ኮንቬንሽኑ ከያዛቸው ነጥቦች ውስጥ-

The Kampala Convention in Brief :- 
- Reaffirms that national authorities have the primary responsibility to provide assistance to internaly displaced people (IDPs)
- Comprehensively addresses
different causes of internal displacement: conflict, generalised violence,
human-caused or natural disasters, and development projects, like building dams or clearing land for large-scale agriculture.
- Recognises the critical role that
civil society organisations, and the communities which take them in, play in
assisting IDPs and obliges governments to assess the needs and vulnerabilities
of the forcibly displaced, and the host communities, in order to address the
plight of people uprooted within their borders,
- It Was adopted by the African Union and currently legally binds 15 African countries to prevent displacement, assist those who have been forced to leave their homes, and find safe and sustainable solutions to help people to rebuild their lives
- A total of 37 African countries have demonstrated their commitment to the convention by
signing it.’’ 
(http://www.internal-displacement.org/kampala-convention).

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዮች ቢሮ አለምአቀፍ የሕግ መርህ በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ሕዝብ አንፃር የሚያስቀምጠው መመርያ(UN Under Secretary-General for Humanitarian Affairs Guiding principles of Internal displacement) አንቀፅ 5 ላይ እንዲህ የሚል ይነበባል- ''All authorities and international actors shall respect and ensure respect for their obligations under international law, including human rights and ons that might lead to displacement of persons.'' humanitarian law, in all circumstances, so as to prevent and avoid conduit'' 
http://www.brookings.edu/~/media/Projects/idp/GPEnglish.pdf.

''በማንኛውም የስልጣን ተዋረድ ያለም ሆነ አልምአቀፍ አካል ሰዎችን  ከሚኖሩበት ቦታ የሚያፈናቅሉ ማናቸውንም ሁኔታዎችን የመከላከል ግዴታ እንዳለባቸው  በሰብአዊም ሆነ አለምአቀፍ ሕጎች መሰረት ይገደዳሉ።'' ይላል።
ኢትዮጵያ ከአውሮፓውያን አቆጣጠር 2000 ዓም ወዲህ የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ቁጥር በእጅጉ ካደገባቸው ሃገራት ትደመራለች።ለእዚህም ዋነኛው መንስኤ የመንግስት የ ጎሳ ፖለቲካን የተከተለ የፌድራል አስተዳደር ዘይቤ መነሻ ያደረገ ግጭት፣መንግስት ለምመሬቶችን ለውጭ ባለሀብት የመሸጥ አወዛጋቢ ፖሊሲ እና አንድ ሕብረተሰብ ላይ ያነጣጠሩ'' የዘር ማፅዳት'' ተግባራት ናቸው።
Trading Economics  የተሰኘ ድህረ-ገፅ ከ 2002 እስከ 2010 ብቻ በኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ የተፈናቀሉትን ተፈናቃዮች ብዛት ከ ሩብ ሚልዮን በላይ መሆናቸውን ይገልፃል።

ባጠቃላይ በቅርቡ በአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ''የዘር ማፅዳት'' ዘመቻ ላለፉት ሃያ አመታት ሲከናወን የነበረ (ብልጭ ድርግም በሚል መልኩ ሲከሰት የነበረ) መሆኑን የምንረዳው ጉዳይ ነው።የምጣኔ ሀብት እድገት በሌለበት መንግስት አድሏዊ አሰራሮች ባሰፈነበት እንደኢትዮጵያ ላለች ሀገር የእዚህ አይነቱ ዜጎችን ለፍተው ጥረው ያገሩትን ንብረት በኃይል ቀምቶ በገዛ ሀገራቸው ስደተኛ ማድረግ አለም አቀፍ ሕግን የጣሰ እና በየደረጃው ያሉ ባለስልጣናት በሕግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩ ምንም አያጠራጥርም።አሁን የሚያስፈልገው መረጃዎችን በበቂ ሁኔታ ማጠናቀር እና መያዝ ነው።
በመጨረሻም የሰሞኑን ድርጊት የተቃወሙ ግለሰብ በተናገሩት ንግግር ፅሁፌን ልደምድም  ‘‘ኤርትራውያን ሲባረሩ ንብረታቸውን በውክልና የመስጠት መብት ያልተነፈጉባት ሀገር እንዴት ዜጎች የገዛ ንብረታቸውን የማውጣት እና የመያዝ መብታቸው ልትነፍግ ቻለች? ሰባራ እንስራም ለእነርሱ ንበረት ነው ያውም ከወፍጮቤት እስከ ትላልቅ ሆቴሎች የተነጠቁትን ትተን  ’’

በአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጉዳያ አገራት ግዴታ የገቡበት ''የካምፓላ ኮንቬንሽን'' ቪድዮ  
Kampala Convention




ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
www.gudayachn.com 

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...