ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, February 24, 2023

በኦሮምያ ክልል ቦረና ህዝብ በድርቅ ይሰቃያል፣እነ አቶ ሽመልስ እና የኦሮምያ ባለስልጣናት ዛሬ በሸራተን አዲስ ሲዝናኑ ውለዋል።የአሁኑ እሁድም ለሌላ ድግስ እየተዘጋጁ ነው።



አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮምያ ክልል ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሰየሙ ቃለ ምህላ ሲፈጽሙ።

በቦረና የደረሰው ድርቅ በተመለከተ:
  • ለአምስት የምርት ወቅት ዝናብ ያልዘነበበት፣
  • ከ3 ነጥብ 3 ሚልዮን በላይ የቀንድ ከብት አልቋል ይህም የክልሉ የከብት ሃብት ከሦስት አራተኛው በላይ አልቋል ማለት ነው።
  • ከሩብ ሚልዮን ህዝብ በላይ ተፈናቅሎ በ21 የመጠለያ ቦታዎች ተጠልሎ ይገኛል፣
  • አሁን እርዳታ አለ በተባለባቸው ቦታዎች ላይ በአማካይ ለስምንት ሰው በወር 15 ኪሎ እህል ለማዳረስ ቢሞከርም ይህ በቂ ባለመሆኑ ህዝብ እያለቀ ነው።

በኦሮምያ ክልል በቦረና የደረሰው ድርቅ እጅግ አስከፊ የድርቅ አደጋ ነው።ድርቁ ለኢትዮጵያ ቁርጥቀን ጊዜ ደራሽ የሆነውን እና ደጉን የቦረና ህዝብ በእዚህ ደረጃ መጉዳቱ ከልብ የሚያሳዝን ነው።የድርቁ አደጋ አስመልክቶ በዋናነት የክልሉ አስተዳደርም ሆነ ፌድራላዊ መንግስት ችግሩን አስመልክተው በተገቢ መንገድ አለመግለጻቸው አሳዛኝ ነው። በተለይ የኦሮምያ ክልል አስተዳደር ክልሉን በምን ያህል የተዝረከረከ መንገድ ብቻ ሳይሆን በህዝብ ህይወት እየቀለደ እንዳለ ያመለክታል። ይህ በእንዲህ እያለ በአቶ ሽመልስ የሚመራው የኦሮምያ ክልል ባለስልጣናት ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል ውሏል።ዛሬ በሸራተን አዲስ የዋሉት እነሽመልስ አብዲሳ በመጪው እሁድም በሌላ ድግስ ላይ እንደሚውሉ ነው የታወቀው። በሁለቱም ቀና የሸገር ከተማ ምስረታ በሚል የሚደረጉ የድግስ ግርግር ላይ የሚሰነብቱት እነሽመልስ እስካሁን ይህ ነው የተባለ የቦረና ድርቅን በተመለከተ የሰጡት መግለጫ የለም። የፌድራል መንግስትም ሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህንኑ ጉዳይ አንስተው መንግስት ምን እየሰራ እንደሆነ ማብራርያ ይሰጣሉ ተብሎ ቢጠበቅም መንግስት እስካሁን ሚዛን የሚደፋ ነገር በጉዳዩ ላይ አልሰጠም። ዛሬ ለመጀመርያ ጊዜ በሚባል ደረጃ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ዜናው ላይ ጉዳዩን አስመልክቶ አንድ ዘገባ አሳይቷል።የኦሮምያ ክልል ባለስልጣናት ግን በድግስ ላይ ድግስ እየደገሱ ከሸራተን እስከ አደባባይ መታየት ላይ ተጠምደዋል። 

ከእዚህ በታች ጀርመን ድምፅ ራድዮ የካቲት 14/2015 ዓም ስለ ቦረና ድርቅ የዘገበው ሙሉ ሪፖርት ያገኛሉ።

በደቡብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እና ሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍሎች የከፋው ድቅር አሁንም መቋጫ አላገኘም፡፡ በነዚህ አከባቢዎች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች ለድጋፍ እጃቸውን ያዘረጋው ድርቁ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የቀንድ እና የጋማ ከብቶችንም ጭምር ገድሏል አስከፊነቱም ቀጥሏል፡፡በደቡብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እና ሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍሎች የከፋው ድቅር አሁንም መቋጫ አላገኘም፡፡ በነዚህ አከባቢዎች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች ለድጋፍ እጃቸውን ያዘረጋው ድርቁ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የቀንድ እና የጋማ ከብቶችንም ጭምር ገድሏል አስከፊነቱም ቀጥሏል፡፡

በተለይም በቦረና በርካታ ከብቶችን በማርባት ለሌሎች ይተርፉ የነበሩት አርብቶ አደሮች አሁን ለድጋፍ ፍለጋ እጃቸውን ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሜትሮሎጂ እንደሚለው ግን ለአምስት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች በድርቅ የቀጠሉት የደቡብ ኢትዮጵያ አከባቢዎች እየመጣ ባለው የዘንድሮ የበልግ ወቅት ለመደበኛ የቀረበ ዝናብ በማግኘት ድርቁ መቋጫ ሊያገኝ ይችላል፡፡ማሊቻ ሞሌ ነዋሪነታቸው በቦረና ዞን ተልተሌ ወረዳ ነው፡፡ በዚህ አከባቢ የሃብትም የኑሮም መገለጫ የሆነው በርካታ ከብቶችን አሰማርቶ መዋል የሳቃቸው ምንጭ የደስታቸውም ጥግ ቢሆንም አሁን ያ ቀርቶ ታሪክ ሆነ ይላሉ፡፡ ምክኒያቱ ደግሞ ከተቋረጠ ወደ አምስተኛ ዙር የዝናብ ወራት እየሄደ ያለው የከፋው ድርቅ አሁንም ድረስ አለማቧራቱ ነው፡፡“ድሮ ባለን መሬት የሆነ ነገር ዘርተን ቢያንስ ለቀለባችን አናጣም ነበር፡፡ አሁን የሚታረስ የለም፡፡ መሬቱ ደርቋል እህል አያበቅልም፡፡ ከከብቶቻችን ቀረን ምንለው የለም፡፡ አሁን ተስፋ ቆርጠን የችግር የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ ካሉኝ የበተሰብ አባላት ያልተራበ ማንም የለም፡፡ እንደውም ሶስቱ የቤተሰቦቼ አባላት በዚሁ ተማረው እግራቸው ወዳመራቸው ሄደዋል፡፡ አሁን ሰው በርሃብ ወደ መሞቱ ነው፡፡ አሁን እዚሁ ጎረቤተ ርሃብ በሚመስል መልኩ ሰው ሞቶ እዛ እያስተዛዘን ነው” ሲሉም ድርቁ እያደረሰባቸው ያለውን የማይገፋ አደጋ በሃዘኔታ ያብራራሉ፡፡

አርብቶ አደር ማሊቻን ጨምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የቦረና ነዋሪዎቹ በተራዘመው ድርቅ አሁን አቅማቸው ተንኩታኩቷል፡፡ ዴንጌ ዋሪዎም በዚሁ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ አሁንስ ተስፋችን ጨልሞ ሰማይ ብናይ ምንም ጠብ ያለ ነገር አጥተናል ከሚሉ ናቸው፡፡

“ታውቃለህ በድርቁ ሰው የካፋ ችግር ውስጥ ነው ያለው፡፡ ያላቸው ከብቶች በግ እና ፍየል እንኳ ሳይቀር አልቀዋል፡፡ ጠብ ያለ ዝናብ ባለመኖሩ የሚወጣ እህል የለም፡፡ የሚሸጥ ከብት በሙሉ በድርቁ አልቀዋል፡፡ አሁን ሰው በችግሩ በህይወት እስከማለፍ ደርሷል፡፡ የሚቀመስ በመጥፋቱ በዚሁ ዓመት ብቻ በዚህች ቀበሌያችን አራት ሰው የሚደርስ ተጎሳቅለው አልፈዋል፡፡ አሁን የሞቱት መጀመሪያ ሰውነታቸው ያብጣል፡፡ ከዚያን ምንም አይነት ምግብ መውሰድ ተስኖያቸው ተጎድተው ይሞታሉ” ሲሉ አስቸጋሪ ያሉት ማህበረሰቡ ያለበትን ችግር አብራርተዋል፡፡

ላለፉት አምስት የዝናብ ወራት ቦረና ምንም አይነት ዝናብ እንዳላገኘ የዞኑ እንስሳት ሃብት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ቃሲም ጉዮ ከዚህ በፊት ለዶይቼ ቬለ በሰጡት ቃለመጠይቅ በከፋ ሁኔታ ቀጥሏል ባሉት ድርቅ በዞኑ ከቤት እንስሳት ብቻ 2.3 ሚሊየን ያህሉ ማለቃቸውን አስረድተዋል፡፡

የዞኑ አስተዳደርም ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንዳመለከተው ከ800 ሺህ በላይ የቦረና ህዝብ አሁን ላይ የእለት ደራሽ ምግብን ይጠባበቃል፡፡ ከቦረና በተጨማሪም ሶማሌ ክልልን ጨምሮ በደቡብ ኢትዮጵያ በተለይም ቆላማዎቹ አከባቢዎች ላይ የከፋው ድርቅ ጉዳትን አስከትሎ በርካቶችን የምግብ ዋስትና አሳጥቷል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት ግን ይህ የደቡብ ኢትዮጵያው ድርቅ ምናልባትም በዚህ ዓመት መቋጫውን ሊያገን ይችላል የሚል ተስፋን ያጫረውን ትንቢያ እየሰጠ ይገኛል፡፡ አሳምነው ተሾመ (ዶ/ር) በኢንስቲትዩቱ የሜትሮሎጂ ትንቢያ እና ቅድመ ማስጠንቀቂያ መሪ ስራ አስፈጻሚ ናቸው፡፡ ከየካቲት እስከ ግንቦት ወራት የሚያጠቃልለው የዘንድሮ የበልግ ወቅት ምንም እንኳ ዘግየት ብልም ለደቡብ ኢትዮጵያ አከባቢዎች በቂ ዝናብን ይዞ ይመጣል ሲሉም ይገልጻሉ፡፡ “ለደቡብ ኢትዮጵያ አብዛኛው አከባቢዎች የበልግ ወራት ዋነኛ የዝናብ ማግኛቸው ወቅት ነው፡፡ በዓመት ከ60 በመቶ በላይ ዝናብ የሚገኙም በዚሁ ወቅት ነው፡፡”

እንደ የሜትሮሎጂ ትንቢያ ባለሙያው ዶ/ር ተሾመ ማብራሪያ፤ ዓለማቀፋዊና አከባቢዊ የአየር ሁኔታዎችን ከግንዛቤ በማስገባት ተዘጋጀ ባሉት የበልግ ወራት የአየር ትንቢያ፤ ከመደበኛው ጋር የተቀራረበ ዝናብ በድርቅ በተመቱቱ የደቡብ ኢትዮጵያ አከባቢዎች ላይ ይኖራል፡፡ “አሁን ላይ የመካከለኛ የፓሲፊክ ውቅያኖስ መካከለኛ አከባቢዎች በላሊና ክስተት ውስጥ መሆኑ ቅዝቃዜ እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ የባህሩ ሙቀት ግን በሂደት ወደ መደበኛ ሁኔታ ይሄዳል፡፡ የህንድ ውቅያኖስም በተመሳሳይ ከቅዝቃዜ ወደ መደበኛ የሙቀት ደረጃ መሄዱ ከግንዛቤ ሲገባ አዎንታዊ የዝናብ መጠን ነው የሚጠበቀው፡፡ እነዚህ ክስተቶች በተለይም በበልግ ወቅት ዝናብ በሚያገኙ የአገራችን አከባቢዎች ብዘገይ ነው እንጂ መደበኛ እና ለመደበኛ የተጠጋ ዝናብ እንዲያገኙ ያስችላል፡፡”

==============/////===========

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።