ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, May 20, 2012

ጋዜጠኛ አበበ ገላው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ እና ሂላሪ ክሊንተን

ሰኔ 11፣2011 ዓም የ አሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂላሪ ክሊንተን አዲስ አበባ በሚገኘው የ አፍሪካ ህብረት ተገኝተው  40 ደቂቃ የፈጀ ንግግር አድርገው ነበር።በንግግራቸው ላይ የ አዲሱ ትውልድን ፍላጎት መስማት አስፈላጊ መሆኑን  እና ሁሉም የ አፍሪካ መሪዎች ቸል እንዳይሉት የመከሩበት ነበር።
ንግግራቸውን በጀመሩ በ ስድስተኛው ደቂቃ ላይ ታድያ የ አዳራሹ መብራት ጠፋ። ቀሪውን ንግግር በድንግዝግዝ መብራት ማንበብ ነበረባቸው። ይህን የሚያህል ትልቅ አዳራሽ ጀነረተር እንደሚኖረው ማንም አይጠራጠርም። የነበረው መብራት ግን (በፊልሙ እንደሚታየው) በግማሽ የተለቀቀ ይመስል ነበር።

 ሂላሪ ክሊንተን  ስለ አፍሪካ ዲሞክራሲ መናገር ሲጀምሩ መብራት በመጥፋቱ የ ኢትዮዽያ መንግስት የ መብራት ሃይል መስርያ ቤት ያልተጻፈ ህግ እንደሚያዘው ''ማስጠንቀቅያ ሳይሰጥ መብራት ማጥፋት ህገ-መብራት ሃይላችን ያዛል''ሊል እንደሚችል የመገመቱን ያህል ባለፈው የ ጂ 8 ጉባዔ ላይ ለ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የ ጋዜጠኛ አበበ ገላው'' ነጻነት!ነጻነት! የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ! አቶ መለስ አምባገነን ናቸው!'' ለሚሉት ድምጾች የ አሜሪካ መንግስት ምላሽ ''የ አሜሪካ ህገ መንግስት ሃሳቡን እንዲገልጽ ይፈቅድለታል ''እንዳለ ለአበበ ፖሊሶቹ ባሳዩት ትህትና አሁንም ይገመታል ።
በሚቀጥለው ቀን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂላሪ  በጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ ውስጥ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ሲነጋገሩ  ከውጭ እንግዳ መቀበያ ክፍል ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ስለነበር ጋዜጠኞች በጉጉት ሲጠባበቁ ነበር። ሆኖም ከንግግራቸው በኋላ በ ሹሉክታ በር ሄዱ።ለምክንያቱ እስካሁን ድረስ  በቂ መልስ የተሰጠ አይመስለኝም። እናም ሂላሪ  አዲስ አበባን ደስ ብሏቸው እንዳለቀቁ ሁሉ አቶ መለስም ዋሽግተንን እንዲሁ።
ጉዳዩ በዲፕሎማሲ ቋንቋ አንድ ለ አንድ ነው እንዴ?
 የ አበበን ሃሳብ በሚጋሩት ዘንድ የማስደሰቱን ያህል የ መለስ አድናቂዎችን በ እጅጉ አናዷል። ቁም ነገሩ ግን ያ አደለም። ወደድንም ጠላንም ግን ለ ኦባማ ጉዳዩ ያን ያህል አያናድዳቸውም። ምክንያቱም ሃሳብን መግለጽ አደለም የተናደደ ጋዜጠኛ  ጫማ የተወረወረበት መሪ ያላት ሃገር ነች- አሜሪካ። የሃገሪቱ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች በ ቀድሞው የ አሜሪካ ፕሬዝዳንት ቡሽ  ላይ ስለተወረወረው ጫማ ከ ኮሜዲ ፊልም ጀምሮ ትልቅ ውይይት አድርገውበታል።

 ወደ እኛ ሃገር ሲመጣ ግን' ተደፈርን' የሚል ስሜት ይዞ ዛቻ እና ማስፈራራት ይጎርፋል። እዚህ ላይ ነው ፈተና ያለው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ
ካሰቡት ወይንም ጉዳዩን ካዩበት እይታ በተለየ እና በላይ 'እኛ ነን የተነካን' ብሎ መናደድ ግን ተገቢ አደለም።  ሁኔታውን በ በቀል እና በ ዛቻ ከመግለጽ በእርጋታ ''ማንም መቶ ከ መቶ ትክክል  የሚባል የለም ስሕተት ምን ላይ ተሰርቷል? ጥፋስ የቱ ላይ ነው ያለው?'' እያሉ መወያየት እና ለወደፊቱ እንደ ሃገር የሚጠቅመን የቱ ነው? ብሎ ማሰብ ነው ጠቃሚው ነጥብ  ።' አንድ ጎል ገባብኝ እኔ ደግሞ ሌላ ጎል  ላግባ' እየተባለ የሚታሰብ ስሌት ህዝብን የሚያጠፋ መሆኑን ማወቅ ብቻ ሳይሆን ማለቅያ የሌለው ያልሰለጠነ ፖለቲካ መገለጫ ሆኖ እንዳይቀር ማሰብ ያስፈልጋል።  ሃሳቦችን በሃሳብነታቸው ላይ መወያየት ግለሰቦቹ (አቶ መለስም ሆኑ አቶ አበበ)  የ ሃሳቡ ተሳታፊዎች ምናልባትም አመንጪዎች መሆናቸው እንደ ገለሰብ በእነርሱ ላይ ብቻ እንዲተኮር ሳይሆን ከእነርሱ ጋር ባሉት ሃሳቦች ላይ መከራከር፣ መነጋገር የ ስልጡን ህዝብ መለያ ነው።


አሁን የተያዘው ግን በሃሳቦች ላይ ከመከራከር ይልቅ በግለሰቦች ላይ ማተኮር ያስመስላል።እናም ግለሰቦችን ትተን ሃሳቦች ላይ መወያየት ብልህነት ነው። አበበም መለስን ሳይሆን ሃሳባቸውን  የመቃወም መብት እንዲኖረው መለስ እና አድናቂዎቻቸውም አበበን ሳይሆን ሃሳቡን ላይ ብቻ ቢያተኩሩ መልካም ነው።ከእዚህ ውጭ ግን 'እኔ ነኝ የተነካሁት' የሚል አስተሳሰብ ከ አፍንጫ እስከ ከንፈር የሚደርስ የጠባብ የሚለው ቃል ቢያንሰው የ ''ጥብቆ'' አስተሳሰብ ነው።እና 'እንሰራለታለን'  በሚል ሃሳብ ከመታጠር በነጥቦቹ ላይ አተኩሮ መወያየት አሁንም ያልለመድነው ግን ልንለምደው የሚገባን ቁም ነገር ነው ።
አበበም 'እንደግለሰብ ከ መለስ ጋር ጸብ የለኝም ሃሳባቸውን ግን እቃወማለሁ' የሚሉት ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ፕሮግራሞች ቢሰራ። እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን በግለሰቦቹ ላይ ብቻ መተኮሩ ትልልቅ ሃሳቦች ተረስተው ጉዳዩ አበበ መለስን እንዲህ አላቸው የሚለው ምን ያህል ጉዳዩን የ ግለሰቦች ጉዳይ አርገው ሊይሽከረክሩት ለሚፈልጉ ሰዎች ከ ግለሰብ ወደ ቡድን ከዚያም በላይ ለማሳደግ ሲያንደረድሩት ይታያችሁ። እናም ሃሳቦቹ ይጉሉ ይነገሩ።
ግለሰቦቹን ስናስታውስ ከመገለጫ ሃሳቦቻቸው ጋር እንጂ ለብቻቸው አናንሳቸው። አበበ ሃሳቡን እዚህ ስብሰባ ላይ ባይገልጽ ኖሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩን  የት አግኝቶ ሃሳቡን ሊገልጽ ይችል ነበር? እሳቸውስ ምን ያህል ግልጽ የውይይት ሃሳቦችን ከፉም ለሙም የሚሰሙበት መድረክ አዘጋጅተው (ቢያንስ ኤምባሲዎቹ አመቻችተው) ያውቃሉ? የሚሉትን ጥያቄዎች ለውይይት መነሻነት የማይሆኑበት ምን ምክንያት አለ?  አሜሪካኖች ፕሬዝዳንት ቡሽ ላይ ጫማ ስለወረወረው እና ስለተወረወረበት ሰው ሳይሆን ስለ ጉዳዩ እንዲፈጠር ምክንያት ስለሆነው ስለ ኢራቅ ጦርነት ተወያዩ ቀጥለው ፕሬዝዳንት ኦባማን መርጠው ሰራዊታቸውን ከ ኢራቅ አወጡ።ይህ ሸጋ ሃሳብ ነው።

አበቃሁ
ጌታቸው
 ኦስሎ





3 comments:

Mehari said...

I like your way of observation.
First I was annoyed now after I read your article. I agree with your idea. LEKA NEGER KOYTO SIYAYUT YIBERDAL. ABEBEN EGELHALEHU YALEWN SEW WEDJEW NEBER AHUN GIN TELAHUT.

Anonymous said...

That is right.
Instead of personalizing the issue it is very important to take an issue popular. The question is DEMOCRACY,DEMOCRACY, FREE DOM, FREE DOM, MELES IS DICTATOR!!! This are the issues which are not get a perfect answer up to this second.Thank you Gech!!

Lemlem ze uk said...

By the way I need to share for this blog readers what I get from AWRA AMBA(http://www.awrambatimes.com/?p=965 ).It is Abebe's latest message after the incidence.
Lemlem
UK

Abebe Gelaw Makes a statement on events surrounding the May 18th call for freedom.
Copyright © 2012 Awramba Times. All rights reserved.

Posted by admin on May 23, 2012 0 Comment


Dear Fellow Ethiopians,


Abebe Gelaw


On Friday 18th May 2012, I voiced the anger, frustration and aspiration of the Ethiopian people in front of world leaders at the G8 food security symposium in Washington DC. “Freedom! Freedom! Freedom!,” was the clarion call that I spoke to power. I condemned Meles Zenawi and his dictatorship in front of his pay masters and sponsors.
Ethiopia deserves better than a deceitful tyrant, who is brutally exploiting, abusing, jailing, torturing and killing our brothers and sisters in every corner of Ethiopia. We need freedom. That has been made clear to the whole world.
Following that eventful day, my fellow Ethiopians from around the world have been expressing their feelings. I have been overwhelmed with the response; praises and poems. Some are calling me a hero, others say I deserve honor. While I appreciate all the outpour of support, this is not about me. It is not about my heroism but the truth that must be told with utmost clarity. It is about our country, every ordinary Ethiopian and the freedom and dignity we deserve. The time has come to claim our God-given rights that nobody can take away, grant or deny.
Let us focus on the ultimate prize. We have to finish the job and declare our freedom. Then we can also proudly sing together as Ethiopians, equal as citizens, “Free at last, free at last…Thank God Almight we are free at last.”
I will say and write more about this and the next steps.
I thank you so much for your support.
Ethiopia shall be free!
Humbly yours
Abebe Gellaw

Copyright © 2012 Awramba Times. All rights reserved.